DCunitedfc

ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቅርቡ ወደ አሜሪካ አቅንቶ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን አድርጎ ተመልሷል። ፌዴሬሽኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአሜሪካ ቆይታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ብሔራዊ ቡድኑ በአሜሪካ ቆይታው አላማውን እንዳሳካ የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። የዲሲ ዩናይትድ ድርሻ ያላቸው አቶ እዮብ ማሞ ከፌዴሬሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ በቅርቡ ከስምምነት እንደሚደርሱም አቶ ባህሩ ገልጸዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በቅርቡ ወደ አሜሪካ በማቅናት ስምምነቱን ይፈፅማሉም ብለዋል። ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚደረገው ስምምነት ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾች በዲሲ ዩናይትድ የመጫወት እድልን እንዲያገኙ እንደሚያስችል አቶ ባህሩ አክለዋል። ይሁንና የቡድኑ የትጥቅ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አውግቼ እና የፊዚዮቴራፒ ባለሙያው…
Read More