10
Aug
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 የውድድር ዓመት የጨዋታ እጣ ድልድልበአዲስ አበባ ይፋ ሆኗል። በዚህ መሰረት ሀምበርቾ ዱራሜ ከድሬዳዋ ከተማ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታውን የሚያደርጉ ሲሆን ሻሸመኔ ከተማ ከወላይታ ዲቻ፣ ሀዋሳ ከተማ ከፋሲል ከተማ የፊታችን መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ. ም ያደርጋሉ። እንዲሁም አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኢትዮጵያ መድህን ከከባህርዳር፣ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዲያ ሆሳዕና ከመቻ የፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎችን ይጫወታሉም ተብሏል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ካምፓኒ ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ በዕጣ አወጣጥ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉት ለተወዳዳሪ ክለቦች መልካም የውድድር ዓመት እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል። በ2015 የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ስያሜ መብትን ቤትኪንግ ይዞ እንደነበር የገለጹት ስራ አስኪያጁ የ2016 የሊግ…