10
Aug
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል በተከሰተው ጦርነት እና ድጋፍ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል። የማህበሩ ዋና ጸሀፊ አቶ ጌታቸው ተአ እንዳሉት በአማራ ክልል በተከሰተው ጦርነት የቆሰሉ ሰዎች፣ የተጠፋፉ እና ሌሎች ጉዳቶች የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ። በዚህም መሰረት የህክምና እና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመርዳት ቀይ መስቀል ማህበር ተሽከርካሪዎቹን በማንቀሳቀስ ላይ በመሆኑ ተፋላሚ ወገኖች ከጥቃት እንዲጠብቁት ማህበሩ ጥሪ አቅርቧል። በቀይ መስቀል ተሽከርካሪዎች የጦር መሳሪያ፣ ወታደሮችን እና ታጣቂዎችን ማጓጓዝ ክልክል መሆኑን የገለጸው ማህበሩ ዓላማችን ተጎጂዎችን መርዳት በመሆኑ ህብረተሰቡ ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጥሪ አቅርቧል። አሁን ላይ የቆሰሉ ሰዎችን ለመርዳት በክልሉ የደም እጥረት እና የህክምና ቁሳቁስ እጥረት በማጋጠሙ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ በጎ…