ዜና

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በአማራ ክልል ያለው አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገለጹ

የተለያዩ አገራት በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ኹከትና የዜጎች ሞት እንዳሳሰባቸው ገለጹ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት ልዑክን ጨምሮ የተለያዩ አገራት ኤምባሲዎች ሰሞኑን በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ኹከት፣ የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ በኢትዮጵያን እና የኦስትሪያ፣ የቤልጂየም፣ የቼክ ሪፖብሊክ፣ የዴንማርክ ፣ የፊንላንድ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርን፣ የሃንጋሪ፣ የአየርላንድ ፣ የኢጣሊያ፣ የሉክሰምበርግ፣ የማልታ፣ የኔዘርላንድስ፣ የሮማኒያ፣ የፖላንድ፣ የፖርቱጋል፣ የስሎቬንያ፣ የስፔን እና የስዊድን ኤምባሲዎች የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታን አስመልክተው የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም በክልሉ የተቀሰቀሰው ኹከት፣ የዜጎች ሞትና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው የገለጹ ሲሆን፤ ኹሉም ወገኖች ሲቪሎችን እንዲጠብቁ፣ ጉዳት ለደረሰባቸው ህዝቦች የተሟላ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀጣይነት ያለው ሰብአዊ ተደራሽነት እንዲረጋገጥ፣ የውጪ ዜጎች ከግጭቱ አካባቢ ለቅቀው እንዲወጡ እና ደህንነቱ በተጠበቀ…
Read More
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል አምቡላንሶቹ ከጥቃት እንዲጠበቁለት ጠየቀ

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል አምቡላንሶቹ ከጥቃት እንዲጠበቁለት ጠየቀ

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በአማራ ክልል በተከሰተው ጦርነት እና ድጋፍ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል። የማህበሩ ዋና ጸሀፊ አቶ ጌታቸው ተአ እንዳሉት በአማራ ክልል በተከሰተው ጦርነት የቆሰሉ ሰዎች፣ የተጠፋፉ እና ሌሎች ጉዳቶች የደረሰባቸው ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ። በዚህም መሰረት የህክምና እና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመርዳት ቀይ መስቀል ማህበር ተሽከርካሪዎቹን በማንቀሳቀስ ላይ በመሆኑ ተፋላሚ ወገኖች ከጥቃት እንዲጠብቁት ማህበሩ ጥሪ አቅርቧል። በቀይ መስቀል ተሽከርካሪዎች የጦር መሳሪያ፣ ወታደሮችን እና ታጣቂዎችን ማጓጓዝ ክልክል መሆኑን የገለጸው ማህበሩ ዓላማችን ተጎጂዎችን መርዳት በመሆኑ ህብረተሰቡ ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጥሪ አቅርቧል። አሁን ላይ የቆሰሉ ሰዎችን ለመርዳት በክልሉ የደም እጥረት እና የህክምና ቁሳቁስ እጥረት በማጋጠሙ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ በጎ…
Read More
በአዲስ አበባ ግብረሰዶም ይፈምባቸዋል የተባሉ መዝናኛ ቤቶች ታሸጉ

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም ይፈምባቸዋል የተባሉ መዝናኛ ቤቶች ታሸጉ

አዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በከተማዋ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚፈጸምባቸው ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ፖሊስ እርምጃውን እየወሰደባቸው ያሉት ሆቴሎች፣ ባሮችና ሬስቶራንቶች ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር እንደሆነ ገልጿል። የተመሳሳይ ጾታ መዝናና ቤቶች ከነባሩ የሀገሪቷ ባህል፣ ወግ፣ የአኗኗር ስርዓት እና ኃይማኖቶች ባፈነገጠ መልኩ ወንጀሎች ይፈጸምባቸው ነበርም ተብላል። ፖሊስ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚያስፈጽሙ ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ፔንሲዮኖችና መሰል የመዝናኛ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ከህብረተሰቡ ጥቆማ እንደደረሰውም አስታውቋል ። የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የግብረ-ሰዶም ተግባር መፈጸምና ማስፈጸም በኢትዮጵያ በሥራ ላይ ባሉ ሕጎች የተከለከለ ናቸው ብሏል። ፖሊስ የተመሳሳይ ጾታ መዝናኛ ቤቶች ባለቤቶች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየታጣራባቸው እንደሆነም አስታውቋል።
Read More
ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቅርቡ ወደ አሜሪካ አቅንቶ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን አድርጎ ተመልሷል። ፌዴሬሽኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአሜሪካ ቆይታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ብሔራዊ ቡድኑ በአሜሪካ ቆይታው አላማውን እንዳሳካ የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። የዲሲ ዩናይትድ ድርሻ ያላቸው አቶ እዮብ ማሞ ከፌዴሬሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ በቅርቡ ከስምምነት እንደሚደርሱም አቶ ባህሩ ገልጸዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በቅርቡ ወደ አሜሪካ በማቅናት ስምምነቱን ይፈፅማሉም ብለዋል። ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚደረገው ስምምነት ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾች በዲሲ ዩናይትድ የመጫወት እድልን እንዲያገኙ እንደሚያስችል አቶ ባህሩ አክለዋል። ይሁንና የቡድኑ የትጥቅ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አውግቼ እና የፊዚዮቴራፒ ባለሙያው…
Read More
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድር መርሀ ግብር ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድር መርሀ ግብር ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 የውድድር ዓመት የጨዋታ እጣ ድልድልበአዲስ አበባ ይፋ ሆኗል። በዚህ መሰረት ሀምበርቾ ዱራሜ ከድሬዳዋ ከተማ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታውን የሚያደርጉ ሲሆን ሻሸመኔ ከተማ ከወላይታ ዲቻ፣ ሀዋሳ ከተማ ከፋሲል ከተማ የፊታችን መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ. ም ያደርጋሉ። እንዲሁም አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኢትዮጵያ መድህን ከከባህርዳር፣ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዲያ ሆሳዕና ከመቻ የፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎችን ይጫወታሉም ተብሏል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ካምፓኒ ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ በዕጣ አወጣጥ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉት ለተወዳዳሪ ክለቦች መልካም የውድድር ዓመት እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል። በ2015 የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ስያሜ መብትን ቤትኪንግ ይዞ እንደነበር የገለጹት ስራ አስኪያጁ የ2016 የሊግ…
Read More
አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በበርካታ ቴአትሮች ፣ ፊልሞች እና የቴሌቭዥን ድራማዎች ላይ በተዋናይነት በመሳተፍ እውቅናን ያተረፈው አርቲስት አብነት ዳግም በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ አርቲስት አብነት ለረዥም ጊዜ በከባድ የስኳር በሽታ ታምሞ የቆየ ሲሆን፤ ትናንት ሕመሙ በርትቶበት ወደ ጤና ጣቢያ ቢወሰድም ሕይወቱን ማዳን ሳይቻል በመቅረቱ ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል፡፡ አርቲስት አብነት አሉላ አባነጋ፣ የቼዝ ዓለም፣ ዳኛው፣ እስረኛው ንጉስ እና ነቅዕ ቴአትሮች ላይ ተውኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አያስቅም፣ አንድ እድል፣ ላምባዲና፣ ሰበበኛ፣ ባንቺ የመጣ፣ ቁልፉን ስጭኝ፣ የነገርኩሽ እለት፣ ፍቅር እስከ መቃብር እና አትሸኟትም ወይ በተሰኙ ፊልሞች ላይ በመተወን አድናቆትን አግኝቷል። ስንቅ ፣መለከት፣ ትርታ እና ለወደዱት ደግሞ የተሳተፈባቸው ቲቪ ድራማዎች ሲሆኑ፤ በግሉም የቅብብሎሽ ድራማን ደርሷል።
Read More
በጎንደር እና ባህርዳር ያሉ ከአንድ ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ

በጎንደር እና ባህርዳር ያሉ ከአንድ ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገለጹ

በአማራ ክልል በተለይም ከአንድ ሳምንት በፊት አንስቶ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል፡፡ በሱዳን በተከሰተው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት የተሻለ ደህንነት ፍለጋ በሚል በተማ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሱዳናዊያን ዜጎች ችግር ውስጥ መግባታቸውን ለአልዐይን ተናግረዋል፡፡ በተለይም በጎንደር እና በባህርዳር ባሉ ሆቴሎች የቆዩ ሱዳናዊያን በምግብ እጥረት፣ ደህንነት እና ትራንስፖርት ችግር  ገጥሞናልም ብለዋል፡፡ ቁጥራቸው ከአንድ ሺህ በላይ እንደሚሆኑ የነገሩን እነዚህ ሱዳናዊያን መንገደኞች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከዚያም ወደ ሳውዲ አረቢያ እና ሌሎች ሀገራት የመጓዝ አቅድን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ተናግረዋል፡፡ ሱዳናዊያኑ በተለይም ከጎንደር እና ብህርዳር ከተሞች ውስጥ ባሉ ሆቴሎች ከተጠለሉት በተጨማሪም በመተማ በኩል አድርገው ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ከገቡ በኋላ…
Read More
በኢትዮጵያ የተቀበሩ ፈንጂዎች ፈንድተው 23 ህጻናት መገደላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተቀበሩ ፈንጂዎች ፈንድተው 23 ህጻናት መገደላቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመት የነበረው ጦርነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተፈረመ ስምምነት መሰረት ማብቃቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እንዳለው ሲቪል ሰዎች በሚኖሩባቸው አካባቢዎች ፣ በእርሻ ፣ በውሃ መቅጃ እና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም የትምህርት ወይም የጤና ተቋማትን የመሳሰሉ የዕለት ተዕለት መሠረታዊ ሕይወት ወደሚከወኑባቸው ሥፍራዎች በሚወስዱ መንገዶች አካባቢ የተቀበሩ ፈንጂዎች ፣ የተጣሉ ቦምቦች ፣ የከባድ መሣሪያ ቅሪቶች እና በቀላል ንክኪ የሚፈነዱ ሌሎች መሣሪያዎች በሰዎች ሕይወት ፣ አካልና ንብረት ላይ ጉዳት እያደረሱ ይገኛል ብላል። ኮሚሽኑ ይህን በተመለከተ ባደረገው ክትትል በአፋር ክልል ፣ ካሳጊታ ከተማ በአንድ መኖሪያ አካባቢ በድንገት በፈነዳው የሞርታር ጥይት ምክንያት 4 ሰዎች ወዲያው ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን በከፍተኛ ደረጃ የአካል ጉዳት…
Read More
በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነት ለአመታት የተጠራቀመ ብሶት ውጤት እንደሆነ ተገለጸ

በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነት ለአመታት የተጠራቀመ ብሶት ውጤት እንደሆነ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) ጦርነቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት ድንገት የተከሰተ ሳይሆን መንግሥት ሃላፊነቱን በተገቢው ሁኔታ ባለመወጣቱ የተከማቹ ሀገራዊ የፖለቲካ ትኩሳቶች የግለታቸው ጫፍ ላይ ሲደርሱ የተፈጠረ ነው ብሏል። ፓርቲው በመግለጫው ይህ ለዓመታት የታመቀው ብሶት፣ የመጠቃት ስሜት እና ተስፋ መቁረጥ ገደፉን አልፎ ክልሉን አሁን ላለበት ሁኔታ ዳርጎታል ሲልም አመልክቷል፡፡ የዚህ ቀውስ መሠረታዊ ምክንያት በብልፅግና ውስጥ ያለው የጋራ ራዕይ መጥፋት፣ በየክልሉ እርስ በእርስ በመጓተት ላይ ያሉ ካድሬዎች የሚመሩት የመንግሥት የአስተዳደር ድክመትና በደል እንደኾነ ሊታወቅ ይገባል ሲልም ገልጾታል። ችግሩን ለማባባስ ፅንፈኛ የዘውጌ ፖለቲካ አስተሳስብን የሚያቀነቅኑ ታጣቂ ኃይሎች በጠራራ ፀሀይ ሰዎችን በመግደል ሽብርና ፍርሃት በመንዛት እንዲሁም ከግል ትርፋቸው ውጪ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አማራ ክልል የሚያደርጋቸውን በረራዎች ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አማራ ክልል የሚያደርጋቸውን በረራዎች ሰረዘ

አየር መንገዱ በድረገጹ እንዳስታወቀው ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ባህርዳር እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ወደሥፍራው ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ መንገደኞች ትኬታቸው ለአንድ ዓመት ያህል የሚያገለግል መሆኑን አውቃችሁ ወደፊት በፈለጋችሁት ቀን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ መቀየር ትችላላችሁም ብሏል፡፡ ገንዘቡን መመለስ እንፈልጋለን ለሚሉ ደንበኞችም ገንዘብ መመለስ እንደሚቻል ገልጾ በአቅራቢያችሁ ባሉ የአየር መንገዱ ቲኬት ቢሮዎች በመሄድ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚቻልም አስታውቋል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል…
Read More