24
Oct
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ በተቀሰቀሰ ጉንፋን መሳይ ወረርሽኝ በአንድ ቀበሌ ብቻ የ78 ሰዎች ህይወት አልፏል። የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ በበኩሉ የወረርሽኙን መከሰት አረጋግጦ አፋጣን ምላሽ ለመስጠት እየጣረ መሆኑን አስታውቋል። ወረርሽኙ ከምዕራብ ወለጋ በተጨማሪ ቄለም ወለጋ ውስጥ መከሰቱንም ዶይቼ ቬለ ከነዋሪዎች አረጋግዐጫለሁ ብሏል፡፡ በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ የሌሊስቱ ሎጲ ቀበሌ ነዋሪ እንደሚሉት በአካባቢው መቋጫ የታጣለት የጸጥታ ችግር ነዋሪውን ለረሃብ እና የወረርሽኝ በሽታ አጋልጦ በርካቶችን ለህልፈት እየዳረገ ነው። “አሁን እኛ ጋ ከፍተኛ የምግብ እጦት ይስተዋላል፡፡ ይህም መነሻው ድርቅ አጋጥሞን አሊያም በፋጣሪ ቁጣ ሳይሆን ሰው በፈጠረው ግጭት ወጥቶ ማረስ አይደለም ወጥቶ መግባቱ ፈተና ሆኖ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡ በኦሮሚያ ክልል…