Rabies

በአዲስ አበባ 18 ሰዎች በእብድ ውሻ በሽታ መሞታቸው ተገለጸ

በአዲስ አበባ 18 ሰዎች በእብድ ውሻ በሽታ መሞታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ 1ሺህ 500 ሰዎች በውሾች ተነክሰዋል ተብሏል ራቢስ በተሰኘ ቫይረስ አማካኝነት በሚከሰተው የእብድ ውሻ በሽታ የተነሳ ባለፋት ስምንት ወራት በአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ የ18 ሰዎች ህይወት ማለፋን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል። በኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ነክ በሽታዎች ምርምር ዲቪዥን ክፍል ተመራማሪ አቶ መስፍን አክሊሉ እንደተናገሩት እንደ አዲስ አበባ ባሉ ከተሞች የውሾች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ይገኛል። በተለይም ደግሞ ባለቤት አልባ ውሾችን በማስወገድ በኩል በቂ ስራ ባለመሰራቱ ሁኔታውን እንዲባባስ አድርጓል።ባለፋት ስምንት ወራት በአዲስ አበባና አካባቢዋ የሚገኙ 1462 ሰዎች የውሻ ንክሻ እንዳጋጠማቸውና ክትባት እንደወሰዱ የተናገሩት  ተመራማሪው በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን ይህን በሽታ ለመግታት ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በጋራ መስራት…
Read More
የእብድ ውሻ በሽታ በየዓመቱ ከ2700 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገድል ተገለጸ

የእብድ ውሻ በሽታ በየዓመቱ ከ2700 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገድል ተገለጸ

የግብርና ሚንስቴር እንደገለጸው በኢትዮጵያ የእብድ ውሻ በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባበሳ እና ስጋት እየሆነ በመምጣቱ  በዓመት እስከ 2 ሺህ 7 መቶ የሚደርሱ ሰዎች ይሞታሉ። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ጤናና ፐብሊክ ሄልዝ ስራ አስፈጻሚ ዶክተር  ውብሸት ዘውዴ እንደተናገሩት ሁኔታው አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልል ከተሞች ትልቅ ስጋት ሆኗል፡፡ በከተሞች አካባቢ ባለቤት አልባ ውሾች በየመንገዱና በየጎዳናው የሚስተዋሉ በመሆናቸው  በርካታ ሰዎች በእብድ ውሻ በሽታ ተጠቂ እየሆኑ ነው ተብሏል። እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑ ህጻናት በበሽታው በስፋት እንደሚጠቁም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በሽታውን ለመከላከል እስከ 70 በመቶ የሚደርሱ ውሾች ቢከተቡ በሽታው ከውሻው ወደ ሰዎች እንዳይተላለፍ ማድረግ እንደሚቻልም ተገልጿል። አስቀድሞ በሽታው በሰዎች ህይወትና ደህንነት ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል  ኢትዮጵያ…
Read More