ዜና

የማራቶን አትሌቶች አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ኢትዮጵያ የሸለመቻቸውን 2 ሚሊዮን ብር አልቀበልም አሉ

የማራቶን አትሌቶች አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ ኢትዮጵያ የሸለመቻቸውን 2 ሚሊዮን ብር አልቀበልም አሉ

በፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ልዑክ ቡድን በብሄራዊ ቤተ መንግስት አቀባበል እና የእራት ግብዣ ተደርጎለታል። ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በተካሄደው የአቀባበል እና የአውቅና ስነ ስርዓት ላይም ለአትሌቶች፣ አሰልጣኞች እና ለታሳታፊዎችዎች እንደየ ተሳትፏቸው እና አብርክቷቸው ከ50 ሺህ ብር እስከ 7 ሚሊየን ብር የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷል። በዚህ ስነ ስርዓት ላይ በማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን ወርቅ ሜዳሊያ ላስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ 7 ሚሊየን ብር እና ወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል። የብር ሜዳልያ ላመጡት አትሌት ትግስት አሰፋ፣ አትሌት በሪሁን አረጋዊ እና አትሌት ፅጌ ዱጉማ ለእያንዳንዳቸው የ 4 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። የታምራት ቶላ እና ትግስት አሰፋ አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ በስነ ስርዓቶ ላይ የ2 ሚልዮን ብር…
Read More
በፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ 

በፓሪስ ኦሎምፒክ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ 

ለ17 ቀናት በፓሪስ የተካሄደው 33ኛው ኦሎምፒክ ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል። በፓሪስ ኦሎምፒክ ድል ያስመዘገቡ እና የተሳተፉ የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን ዛሬ ማለዳ ነሀሴ 7 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ገብተዋል። የልኡካን ቡድኑ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በዛሬው እለት ከሰዓት በኋላ በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በተገኙበት ለልዑካን ቡድኑ የክብር ሽልማት፣ የማበረታቻ እና የእራት ግብዣ መርኃ-ግብር የሚካሄድ መሆኑንም ተገልጿል። ኢትዮጵያ በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ 1 የወርቅ እና 3 የብር በአጠቃላይ 4 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ከዓለም 47ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 4ኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወቃል። ታምራት ቶላ በማራቶን ወርቅ፣ ጽጌ ድጉማ በሴቶች 800 ሜትር ብር፣ በሪሁ አረጋዊ በወንዶች 10 ሺህ…
Read More
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ሁለተኛውን ዙር ድርድር በአንካራ ጀመሩ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ሁለተኛውን ዙር ድርድር በአንካራ ጀመሩ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ከወደብ ጋር በተያያዘ በመካከላቸው የተፈጠረዉን ዉጥረት ለመፍታት ሁለተኛ ዙር ድርድራቸውን በአንካራ ጀምረዋል፡፡ የቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይፕ ኤርዶሃን በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ንትርክ ዙሪያ ከፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ጋር በስልክ መምከራቸውም ተሰምቷል፡፡ የቱርክ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይፕ ኤርዶሃን ከሶማሊያ አቻቸዉ ሀሰን ሼክ ማህሙድ ጋር በስልክ መምከራቸዉ ተዘግቧል። በቱርክ እና በሶማሊያ መካከል ያለውን ትብብር አስፈላጊነት በማጉላት አንካራ ፥ በሞቃዲሾ እና በአዲስ አበባ መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ጥረቷን እንደምትቀጥል የቱርክ ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በኤክስ ገጹ ላይ ጽፏል። በዛሬዉ እለት በቱርኪዬ ርዕሰ መዲና አንካራ ከሚካሄደው ሁለተኛ ዙር የሶማሊያ እና የኢትዮጵያ ድርድር ውጥረቱን ለማርገብ ተጨባጭ ውጤት ይጠበቃል ብሏል። መሪዎቹ በስልክ ዉይይታቸዊ በሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም በአህጉራዊ እና…
Read More
ኢትዮጵያ በሐምሌ ወር በታሪክ ከፍተኛ መጠን ያለው ቡና ወደ ውጭ መላኳ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሐምሌ ወር በታሪክ ከፍተኛ መጠን ያለው ቡና ወደ ውጭ መላኳ ተገለጸ

ኢትዮጵያ እስከ ዛሬ ድረስ በአንድ ወር ውስጥ ለሽያጭ ካቀረበችው ቡና በአዲሱ የ2017 በጀት አመት ሀምሌ ወር ከፍተኛ ገቢ ማግኘቷ ተሰምቷል፡፡ በ2017 በጀት አመት ሀምሌ ወር ከቡና ሽያጭ ከ180 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳህለማርያም ገብረ መድህን እንደተናገሩት  ይህ አፈጻጸም እስከዛሬ ድረስ  በሁሉም የሀምሌ ወራት  ከተገኘው ገቢ  ጋር ሲነጻጸር ሪከርድን የሰበረ ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ሀምሌ ወር ለውጪ ገበያ ከቀረበዉ 40 ሺህ 532 ቶን ቡና ከ180 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል፡፡ በዚህም  እስከዛሬ ድረስ በአንድ ወር ውስጥ ለውጭ ገበያ  ቀርቦ ከተገኘው  ገቢ አኳያ ሲነጻጸር ሪከርድን  መስበር ችሏል፡፡ከእቅድ አንፃር …
Read More
በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ፍትህ እንዲያገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ጥሪ አቀረበ

በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ፍትህ እንዲያገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ጥሪ አቀረበ

መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ፍትህ እንዲያገኙ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበር ጠይቋል። ማህበሩ የጋዜጠኞቹ የፍርድ ሂደትም ከፖለቲካ አተያይ በፀዳ መንገድ እንዲሆን ጥሪውን ያቀርባል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር አዲስ ሥራ አስፈጻሚ አባላት በአዲ አበባ ቃሊቲና ቂሊንጦ ማረሚያ ቤቶች በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸውም ስለ ማረሚያ ቤት አያያዝ እና አጠቃላይ የፍትህ ሂደቱ ያለበትን ሁኔታ ከጋዜጠኞቹ ጋር እንደተወያዩ ማህበሩ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል፡፡ ጋዜጠኞቹ በማረሚያ ቤቶቹ አያያዝ በኩል ቅሬታ ባይኖራቸውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር በተያዙበት ወቅት የተያዙበት መንገድም ሆነ ከተያዙ በኃላ ያለው የፍርድ ቤት ሂደት አግባብነት እንደሚጎድለው ተናግረዋል፡፡ በሁለቱም ማረሚያ ቤቶች ከአንድ ዓመት በላይ ሳይፈረድባቸው የታሰሩ ጋዜጠኞች መኖራቸውን ማኅበሩ እንዳረጋገጠ አስታውቋል። ስለሆነም…
Read More
ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

በየ አራት አመቱ አንዴ የሚካሄደው የኦሎምፒክ ውድድር በፓሪስ ሲካሄድ 15ኛ ቀኑን ይዟል። 206 ሀገራት በሚሳተፉበት በዘንድሮው ውድድር ከ10 ሺህ 500 በላይ አትሌቶችም እየተሳተፉበት ይገኛል፡፡ ዛሬ ረፋድ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ውድድር አትሌት ታምራት ቶላ ርቀቱን በ2:06:26 በሆነ ሰዓት አሸንፏል፡፡ አትሌት ታምራት ቶላ ውድድሩን የጨረሰበት ሰዓት አዲስ የኦሎምፒክ ክብረ ወሰን በማስመዝገብ እንዳሸነፈም ተገልጿል፡፡ ውድድሩን ቤልጂየማዊው በሽር አብዲ ሁለተኛ እንዲሁም ኬንያዊው ቤንሰን ኪፕሩቶ ደግሞ ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ አትሌት ታምራት ቶላ ከውድድሩ በኋላ እንዳለው "ውድድሩን በማሸነፌ እና የወርቅ ሜዳልያውን ለሀገሬ ኢትዮጵያ በማስገኘቴ በጣም በጣም ተደስቻለሁ" ሲል በእምባ ታጅቦ አስተያየቱን ሰጥቷል። አትሌት ታምራት ቶላ በውድድሩ በ2:06:26 በሆነ ሰዓት በመግባት በወንዶች ማራቶን የኦሎምፒክ ሪከርድ ባለቤት መሆን…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 100 ሚሊዮን መንገደኖችን የሚያስተናገድ ኤርፖርት ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 100 ሚሊዮን መንገደኖችን የሚያስተናገድ ኤርፖርት ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ ለመገንባት በሂደት ላይ መሆኑን አስታውቋል። በዓመት 100 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው አውሮፕላን ጣቢያ በቢሾፍቱ ከተማ እንደሚገነባ ገልጿል። ይህ አውሮፕላን ጣቢያ ወይም ኤርፖርት የሚገነባው በዓመት 25 ሚሊዮን መንገደኞችን ብቻ የማስተናገድ ያለው ቦሌ ዓከም አቀፍ ኤርፖርትን ለመተካት እንደሆነ የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል። በቢሾፍቱ ልዩ ስሙ አቡ ሴራ በተባለው ስፍራ የሚገነባው ይህ ኤርፖርት ግንባታ ዲዛይን ዳር የተሰኘው ኩባንያ መመረጡንም አቶ መስፍን ገልጸዋል። አቶ መስፍን አክለውም አዲሱ ኤርፖርት ግንባታ በአምስት ዓመታት ውስጥ በሁለት ዙር ይገነባል ያሉ ሲሆን ለመጀመሪያው ዙር ግንባታ ስድስት ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታልም ብለዋል። ኤርፖርቱ ባንድ ጊዜ አራት አውሮፕላኖችን የማሳረፍ እና መንደርደሪያ…
Read More
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክተዋል። የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክታለች። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለአሜሪካዊያን አገልግሎት የሰጡ ተቋማትን እና ግለሰቦችን የህይወት ዘመን ሽልማት ይሰጣል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 25 ዓመታት በአሜሪካ ለሚኖሩ ዜጎች በሰጠው አገልግሎት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኗል። አየር መንገዱ ሽልማቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ "ሽልማቱ ለሰጠው አገልግሎት እውቅና የሰጠ ነው" ብሏል። ፕሬዝዳንት ባይደን የፈረሙበት ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮች በአትላንታ በተዘጋጀ መርሀግብር ላይ ተቀብለዋል ተብላል። የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱ ባለፉት ዓመታት ለሰጠው የአቪዬሽን አገልግሎት እውቅና ባለፈ ዓለም አቀፍ ትብብሮችን እንዲያሰፋ…
Read More
አዲስ አበባ ዓለም-አቀፍ የቦክስ ውድድር ልታስተናግድ ነው

አዲስ አበባ ዓለም-አቀፍ የቦክስ ውድድር ልታስተናግድ ነው

የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌደሬሽን ዋና ቢሮውን በአዲስ አበባ የከፈተ ሲሆን፣ ቅዳሜ ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በደማቅ ዝግጅት በይፋ ያስመርቃል፡፡ ፌዴሬሽኑ የቢሮውን መክፈት አስመልክቶ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ አለም አቀፍ የቦክስ ውድድር እንደሚዘጋክ ተገልጿል፡፡ ይህ አለም አቀፍ የቦክስ ውድድርን የአለም አቀፉ የቦክስ ማህበር ከአፍሪካ የቦክስ ኮንፌደሬሽን እንዲሁም ከኢትዮጵያ የቦክስ ፌደሬሽን ጋር በመተበበር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይዘጋጃል ተብሏል፡፡ 20 ዓለም አቀፍ ፕሮፌሽናል ቦክሰኞች ከሩሲያ፣ ሜክሲኮ፣ እንግሊዝ፣ ካዛኪስታን፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተገልጿል፡፡ ይህ ልዩ የቦክስ ውድድር ላይ የተሳተፉ ቦክሰኞች በአፍሪካ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቶላቸዋል የተባለ ሲሆን ውድድሩ በ10 ዘርች ይካሄዳል ተብሏል፡፡ ይህ አለም-አቀፍ የቦክስ ውድድርን ለመዘገብ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላርን በ107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላርን በ107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ  ባንክ ለባንኮች ዶላር ለመሸጥ ያወጣው ልዩ ጨረታ ውጤትን ይፋ አድርጓል። በዛሬው እለት በተካሄደው ልዩ ጨረታ 27 ባንኮች የሚፈልጉትን የዶላር መጠን እና የሚገዙበትን ዋጋ አስገብተው ተጫርተዋል። ባንኮቹ ለአንድ የአሜሪካ ዶላር ያቀረቡት አማካይ የመግዣ ዋጋ 107.9 ብር መሆኑን ባንኩ ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ጨረታው በነገው እለት ባንኮች በሚያወጡት እለታዊ የውጭ ምንዛሬ ተመን ላይ ለውጥ እንዲመጣ እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብሏል ብሔራዊ  ባንክ። የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ የዶላር ሽያጭ ጨረታው ውጤትን ሲገልጹ ባለፉት ቀናት በባንኮች እና በብላክ ገበያው መካከል ያለው ልዩነት እየጠበበ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የውጭ ምንዛሬ መረጋጋትን ያመጣል ያሉት አቶ ማሞ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሁሉንም የውጭ ምንዛሬ እንቅስቃሴ ወደ ባንክ ስርአት የማስገባት እቅድ…
Read More