Blog

በአዲስ አበባ ያሉ የገበያ ቦታዎችን በአንድ ቦታ የሚያገኙበት ሞል ኢን አዲስ የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ ሆነ፡፡

በአዲስ አበባ ያሉ የገበያ ቦታዎችን በአንድ ቦታ የሚያገኙበት ሞል ኢን አዲስ የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ ሆነ፡፡

ሜልፋን ቴክ በተሰኘ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ኩባንያ የተሰራው ሞል ኢን አዲስ መተግበሪያ በወጣት ኢትዮጵያዊያን የተሰራ ነው። የመልፋን ቴክኖሎጂ ስራ አስኪያጅ አቶ መልካሙ ምትኩ በፕሮግራሙ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት መተግበሪያው ፈጣን እና የእለት ተዕለት  ህይወታችንን በማቅለል ረገድ ዓይነተኛ ሚና ይጫወታል። መልፋን ቴክ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ ከአምስት አመታት በላይ እየሰራ የሚገኝ ተቋም ከፌደራልና ከክልል አስተዳደሮች፣ ከግልና አንጋፋ ከሆኑ የአገሪቱ ተቋማት ጋር በርካታ ስራዎችን ሲሰራም ቆይቷል ብለዋል። የተለያዩ የሶፍትዌር ስራዎችን፣ የሞባይልና የኮምፒውተር አፕልኬሽኖችን፣ የተቋማትን ሲስተም ማበልፀግን እና ለዲጂታል ኢትዮጵያ እቅድ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። መልፋን ቴክ ከ45 በላይ ለሚሆኑ ባለሙያዎች የስራ ዕድል ፈጥሮ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ድርጅቶች በደንበኝነት አፍርቶ፣ ከ14…
Read More
የአረብ ሊግ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ላንድ ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

የአረብ ሊግ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ላንድ ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከሶስት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ በኤደን ባህረ ሰላጤ 20 ኪሎሜትሮች የሚረዝም የባህር ጠረፍ እንድትከራይ እና በምትኩ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ የሚያስችል ነው። ይህ ስምምነት ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። ይህን ተከትሎም የአረብ ሊግ እና ግብጽን ጨምሮ በርካታ ሀገራት እና ተቋማት የሱማሊያ ሉዓላዊነትን እንደሚያከብሩ ስምምነቱን እንደማይደግፉት ተናግረዋል። የአረብ ሊግ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የሊጉ አባል ሀገራት ውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጉዳይ እንደሚመክር አስታውቋል፡፡ በበይነ መረብ እንደሚካሄድ የተገለጸው ይህ የሚኒስትሮች አስቸኳይ ስብሰባ የፊታችን ረቡዕ እንደሚካሄድ የሊጉ…
Read More
የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

አየር መንገዱ በአፍሪካ ያሉትን የጭነት መዳረሻዎች ብዛት ወደ 35 አሳድጓል። ወደ ካዛብላንካ የሚደረገው የጭነት በረራ ከ100 ቶን በላይ የመሸከም አቅም ባለው ቦይንግ 777-200F የእቃ ጭነት አውሮፕላን ነው ተብሏል። የኢትዮጵ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው “ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት መስጠት በመጀመራችን ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል በመልዕክታቸው። ይህ በረራ መጀመሩ በአፍሪካ ያለንን የዕቃ ጭነት መዳረሻ ቁጥር 35 ሲያደርስ፤ በተመሳሳይ ብሔራዊ አየር መንገዱ በእቃ ጭነት አገልግሎት ዘርፍ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጭነት በረራ መዳረሻዎች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ እና በዓለም የአየር የዕቃ ጭነት አገልግሎት መስክ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ የሚገኝ…
Read More
ኢትዮጵያ በቮልስዋገን ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች

ኢትዮጵያ በቮልስዋገን ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች

በቮልስ ዋገን አይዲ ሲሪየስ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተጥሎ የነበረው እገዳ መነሳቱ ተገልጿል፡፡ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ባሳለፍነው ሰኔ ወር ላይ ቮልስ ዋገን አይዲ ሲሪየስ (ID Series) የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ እገዳ ጥላ ነበር፡፡ ከቻይና ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ የነበረው የጀርመን ምርት የሆነው ቮልስ ዋገን ተሽከርካሪ ባትሪው ከኢትዮጵያ የአየር ንብረት ጋር የሚጣጣም አይደለም በሚል በቀረበው ቅሬታ መሠረት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ታግዶ ቆይቷል፡፡ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሕዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪና ተሽከርካሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አበራ ሞሲሳ እንዳሉት፤ የጀርመን መንግሥት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ መሠረት ቮልስ ዋገን ተሽከርካሪ እንዳይገባ ተደርጎ ቆይቷል፡፡ ደብዳቤው የተሽከርካሪዎች ባትሪ ከኢትዮጵያ የአየር ንብረት ጋር የማይጣጣም…
Read More
በኢትዮጵያ ከ20 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች በሐሰተኛ ሰነዶች እንደሚኖሩ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ20 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች በሐሰተኛ ሰነዶች እንደሚኖሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት እንዳስታወቀው የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅመው ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸውን ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡ የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ሀሰተኛ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ሀሰተኛ ፓስፖርት፣ ሀሰተኛ ቪዛ እና ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅተው በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየኖሩ ይገኛል ብለዋል። በተደረገው የማጣራት ስራ ከ18 ሺህ በላይ ሀሰተኛ ጊዚያዊ የመኖሪያ ፈቃድ፣ ከ1 ሺህ 500 በላይ ሀሰተኛ ቪዛ እና ከአንድ ሺህ 800 በላይ የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያን ያሰሩ ዜጎች በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች መገኘታቸውንም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። በመሆኑም ህገወጥ ሰነድ ያለቸው ዜጎች ከጥር አንድ ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም…
Read More
አሜሪካ እና የአፍሪካ ሕብረት የሶማሊያ ሉዓላዊነት እንዲከበር ጠየቁ።

አሜሪካ እና የአፍሪካ ሕብረት የሶማሊያ ሉዓላዊነት እንዲከበር ጠየቁ።

ኢትዮጵያ ከአራት ቀናት ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ አዲስ ትኩሳት እንዲፈጠር ምክንያት የሆነ ሲሆን ሀገራት በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ ሱማሊላንድ አንድ አካሌ ናት የምትለው ሶማሊያ ስምምነቱን እንደ ወረራ እንደምትመለከተው ገልጻ ተመድ፣ አፍሪካ ህብረት ፣ የአረብ ሊግ እና ሀገራት ከጎኗ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርባለች፡፡ አሜሪካ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ የሰጠች ሲሆን ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና መስጠት ስህተት እንደሆነ ገልጻለች። የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ቃል አቀባይ ማቲው ሚለር እንዳሉት "የሶማሊያን ሉዓላዊነት ከማክበር ባለፈ እውቅና ትሰጣለች፣ በአፍሪካ ቀንድ የተፈጠረው አዲስ ውዝግብም ያሳስበናል" ብለዋል። "ሁሉም አካላት ጉዳዩን ከማካረር ሊቆጠቡ ይገባል" ያሉት ቃል አቀባዩ "አለመግባባቱን በዲፕሎማሲያዊ ድርድር ሊፈቱ ይገባል" ሲሉም አሳስበዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን…
Read More
የኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ አዲስ የዲፕሎማሲ ፍትጊያ መፍጠሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ አዲስ የዲፕሎማሲ ፍትጊያ መፍጠሩ ተገለጸ

በቀይ ባህር ላይ ወደብ እንደሚያስፈልጋት ስትገልጽ የቆየችው ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ማስታወቋ ይታወሳል፡፡ የሁለቱ አካላት የመግባቢያ ስምምነት ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ 20 ኪሎ ሜትር ላይ ወደብ እና ወታደራዊ ቤዝ እንዲኖራት የሚፈቅድ ሲሆን በአንጻሩ ደግሞ ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ ይጠቅሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሶማሊላንድ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ የ20 በመቶ ድርሻ እንዲኖራት ይደረጋል የተባለ ሲሆን በአንድ ወር ውስጥ ተጨማሪ ድርድሮች እንደሚካሄዱ ተገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ሶማሊያ የኢትዮጵያን እና የግዛቴ አካል ናት የምትላት ሶማሊላንድ ያደረጉት ስምምነት ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ዓለም አቀፍ ህግንም የሚጥስ እንደሆነ አስታውቃለች፡፡ ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ያደረጉት ስምምነት ሶማሊያ አልሻባብን ለማጥፋት የጀመረችውን ዘመቻ እንደሚያስተጓጉል እና የሽብር ቡድኑ ዳግም እንዲያንሰራራ እንደሚያደርግም…
Read More
ላለፉት ሶስት ዓመት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የሰላም ስምምነት ፈረመ

ላለፉት ሶስት ዓመት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የሰላም ስምምነት ፈረመ

ላለፉት ሶስት ዓመት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ከአማራ ክልል አስተዳድር ጋር የሰላም ስምምነት ተፈራረመ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የንቅናቄው አመራሮች በተለያዩ የአመራር ቦታዎች ላይ ሹመት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል፡፡ የአገው ዴሞክራሲ ንቅናቄ (አዴን) የጥቅምት 2013ቱን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በተለይም በአበርገሌና ፃግብጂ ወረዳዎች ትጥቅ ትግል ሲያካሄድ ቆይቷል፡፡ ታጣቂ ኃይሉ በሁለቱ ወረዳዎች ቆላማ አካባቢዎች እስከ 19 የሚሆኑ ቀበሌዎችን ሲቆጣጠር እንደነበረም ንቅናቄውና የመንግስት አካላት አመልክተዋል፡፡ የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የመንግሰትን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ ታህሳስ 13 ቀን 2016 ዓ ም በአዲስ አበባ ከተማ ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት ማድረጉንና ትናንት ደግሞ በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ማዕከል ሰቆጣ ከተማ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን ገለጸች

በቀይ ባህር ላይ ወደብ እንደሚያስፈልጋት ስትገልጽ የቆየችው ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ወደብ በሊዝ መግዛቷን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ እንደ ጽህፈት ቤቱ መግለጫ ከሆነ የባህር በር የምታገኝበትን የመግባቢያ ስምምነት ከሶማሌ ላንድ ጋር ተፈራርማለች፡፡ የባህር በር ሊዝ ስምምነቱን ጠቅላይ ሚኒስትር  ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሌ ላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ እንደተፈራረሙ ተገልጿል። የኢትዮጵያ እና ራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስምምነት ኢትዮጵያ የቀይ ባህር በር እንዲኖራት ለያዘችው ጥረት ጥሩ መደላደል ሊፈጥር ይችላልም ተብሏል፡፡ ይሁንና የባህር በር ሊዝ ስምምነቱ ለምን ያህል ጊዜ፣ በምን ያህል ገንዘብ እና የስምምነቱ ዝርዝር መረጃ እስካሁን በማንኛውም ወገን ይፋ አልተደረገም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከወራት በፊት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት…
Read More
ኢትዮጵያ በሕገ- ወጥ እንስሳት ንግድ ምክንት በየወሩ 17 ሚሊዮን ዶላር እያጣች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በሕገ- ወጥ እንስሳት ንግድ ምክንት በየወሩ 17 ሚሊዮን ዶላር እያጣች ነው ተባለ

ኢትዮጵያ በቀን ከ1 ሺህ 200 በላይ የቁም እንስሳት በሕገ-ወጥ መንገድ ከአገር በመውጣታቸው በየቀኑ ከ630 ሺህ ዶላር በላይ እንደምታጣ ተገልጿል። በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገብተው ለአገልግሎት የሚወሉ መድኃኒቶችም የጥራት ደረጃቸውን ያልጠበቁ በመሆናቸው በጤና ሥርዓቱ ላይ ጫና እያሳደሩ መሆኑም ተገልጿል። በኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አዘጋጅነት ሕገ-ወጥ ንግድን መከላከል ላይ ያተኮረ አገር አቀፍ ጉባዔ በአዲስ አበባ ዛሬ ተካሂዷል። ምክር ቤቱ ሕገ-ወጥ ንግድ በስፋት በሚታይባቸው ዘርፎች ላይ ያካሄዳቸውን ጥናቶች ይፋ አድርጓል። ጥናቶቹ በቁም እንስሳት፣ በመድኃኒት፣ በጨርቃጨርቅ፣ በሎጂስቲክስ ሥርዓት ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችና ንግድን በተመለከቱ የሕግ ማዕቀፎች ላይ የተካሄዱ ናቸው። አሁን ላይ የቁም እንስሳትና የመድኃኒት ሕገ-ወጥ ንግድ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ በጥናቱ ተመላክቷል። በኢንዱስትሪ…
Read More