Blog

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩንቨርሲቲዎች ከጥር አንድ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን ሊጠሩ ነው

በአማራ ክልል የሚገኙ ዩንቨርሲቲዎች ከጥር አንድ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን ሊጠሩ ነው

ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ትምህርት ይጀምራሉ ብሏል፡፡ ሚኒስቴሩ አክሎም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር። በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ መቆየቱን ገልጿል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ታህሳስ 18 ቀን 2016 ዓ.ም  በጉዳዩ ዙሪያ መክረዋልም ተብሏል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው…
Read More
አንድ ሺህ ጥንድ ተጋቢ ሙሽሮች በአንድ ቀን በአንድ ቦታ ሊሞሸሩ ነው

አንድ ሺህ ጥንድ ተጋቢ ሙሽሮች በአንድ ቀን በአንድ ቦታ ሊሞሸሩ ነው

ያሜንት ኢቬንትስ ጥንዶችን ለመሞሸር የያዘውን ፕሮጀከት አላማ ለማሳወቅ እና ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በቀጣይ አብሮ በትብብር ለመስራት የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ ያሜንት ኢቭንትስ በዚህ ጊዜ እንዳለው "ቤተሰብን መመስረት ሀገርን መገንባት ነው" በሚል መርህ ጥር 5  ቀን 2016  ዓ.ም አንድ ሺህ ጥንድ ተጋቢዎችን በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ጋብቻ እንዲመሰርቱ የሰርግ ሁነት አዘጋጅቷል። በባህልና ስፖርት ሚኒስቴርና በያሜንት ኢቬንትስ መካከል ዛሬ የተፈረመው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሰነድ የየሺህ ጋብቻ እንደ ሀገር አቀፍ የቤተሰብ ፕሮጀክት እንዲዘልቅ በማድረግ ከቤተሰብ አመሰራረት ጋር የሚገጥሙ ችግሮችን ለማቃለል አላማው ያደረገ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ የጋራ ጋብቻ ሁነት አመታዊ ካርኒቫል የህዝብ ለህዝብ ትስስርንና መተማመንን ከማጠናከር ባሻገር ኢትዮጵያ የምትታወቅበትን ጎብኚዎችን እንዲስብ ለማድረግ መታሰቡም…
Read More
ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ በጋራ አስተዋውቀዋል። አቶ ዮሃንስ ሚሊዮን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን “ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል” በሚል የተሰየመው ይህ አገልግሎት በደንበኞች ምርጫ መሰረት በ6 ወር ወይም በ12 ወር የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል። ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን እንደሚኖርባቸውም ጠቁመዋል።  አቶ ዮሃንስ አክለውም አገልግሎቱን ለማግኘት ደንበኞች አቅራቢያቸው ወደሚገኝ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ በሚያመሩበት ወቅት አስፈላጊ ሰነዶችን ማሟላት የሚገባቸው ሲሆን ማስያዣም ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል። ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና…
Read More
አሜሪካ፣ ካናዳ እና ብሪታንያ ኢትዮጵያ የቬና ዲፕሎማቲክ ስምምነት መጣሷ እንዳሳሰባቸው ገለጹ

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ብሪታንያ ኢትዮጵያ የቬና ዲፕሎማቲክ ስምምነት መጣሷ እንዳሳሰባቸው ገለጹ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው መሰረት በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዳልወሰደ እና ጉዳዩን ስለመመርመሩ መረጃ እንዳልሰጠው ገልጿል፡፡ የአሜሪካ፣ ካናዳ እና ብሪታኒያ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጡት…
Read More
በአማራ ክልል ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን በክልሉ ያለው የጸጥታ ችግር በተማሪዎች ምዝገባ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል ብለዋል። ክልሉ 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር ሲገባው ያን ማድረግ አለመቻሉን ኃላፊው ተናግረዋል። ከሁለት ሚሊዮን በላይ ያልተመዘገቡ ተማሪዎች መኖራቸውን የገለፁት ኃላፊው ፤ መማር የሚገባቸው ተማሪዎች የትምህርት ዕድል እንዳያገኙ መደረጉን አመልክተዋል። በጸጥታው ችግር ምክንያት ሁለት ሺህ በሚጠጉ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን ከመማር ማስተማር ሥራ ውጪ መሆናቸውን ገልፀዋል። ይሁን እንጂ መምህራኑ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ የማድረግ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። በክልሉ ባለው ግጭት "ወደ 42 ትምህርት ቤቶች…
Read More
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን እንደማትፈቀድ አስታወቀች

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን እንደማትፈቀድ አስታወቀች

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ ባሳለፍነው ሰኞ የቤተ-ክርስትያኗ ካህናት ለተመሳሳይ ፆታ ጥንዶች ቡራኬ መስጠት እንዲችሉ ፈቃድ መስጠታቸው ይታወሳል። ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ አዲሱን የቫቲካን መመሪያ የሚያትቱ መዛግብትን ማፀድቃቸውን ተከትሎ ነበር የቤተ-ክርስትያኗ ካህናት ለተመሳሳይ ፆታ ጥንዶች ቡራኬ መስጠት እንዲችሉ ፈቃድ መስጠታቸው የተሰማው። ፖፕ ፍራንሲስ፤ የቤተ-ክርስትያኒቱ ቄሶች የተመሳሳይ ፆታ “ያልተለመዱ” ጥንዶችን በአንዳንድ ሁኔታዎች ቡራኬ መስጠት እንዲችሉ ፈቅጃለሁ ሲሉ ተሰምተዋል። ቫቲካን ይህንን ተከትሎ በሰጠው ማብራሪያ ይህ የሚሆነው በተለምዶ በቤተክርስትያኗ በሚካሄዱ ሥነ-ሥርዓቶች ላይ እንዳልሆነ እና አሁንም ቢሆን ትዳር በአንድ ወንድና ሴት መካከል የሚደረግ ሥነ-ሥርዓት እንደሆነ ነው የምናየው ብሏል። የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽህፈት ቤት በጉዳዩ ላይ ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ፤ የሊቀ ጳጳሱ መልዕክት…
Read More
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል አዲስ ተደራዳሪ ቡድን አዋቀረች

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል አዲስ ተደራዳሪ ቡድን አዋቀረች

የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድርን እና ቀጣናዊ የንግድ ትስስሮችን የሚመራ ብሔራዊ ኮሚቴ በአዲስ መልክ መቋቋሙን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችን እንዲሁም ባለሙያዎችን ያካተተ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን በተለያዩ ጊዜያት ፍላጎቷን ብታሳይም ከአባል አገራት ለሚነሱ አንዳንድ የንግድ ዘርፍ አካታችነት አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ባለመቻሏ ድርጅቱን መቀላቀል ሳትችል ቆይታለች። የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ከአምስት ዓመት በፊት ወደ ስልጣን ሲመጣ የዓለም ንግድን በአባልነት መቀላቀል እንደሚፈልግ በይፋ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ መንግስት ከወሰዳቸው ስር ነቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና አዳዲስ ለውጦች መካከል አገሪቱን በ2021 የአለም ንግድ ድርጅት አባል ማድረግ ይገኝበታል። በዚህም ከ2020 አንስቶ ድርድር እንደ አዲስ…
Read More
ኢትዮጵያ 6 ሚሊዮን ዶላር በስህተት ለሌላ ወገን መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ 6 ሚሊዮን ዶላር በስህተት ለሌላ ወገን መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት ባንክ ዓመታዊ መዋጮ መከፈል የነበረበትን ስድስት ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ በስህተት ወደ ሌላ አካውንት መላኳ ተገልጿል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው…
Read More
ካሊፎርኒያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 102 የዲጂታል ማርኬቲንግ  ሰልጣኞቹን አስመረቀ

ካሊፎርኒያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 102 የዲጂታል ማርኬቲንግ  ሰልጣኞቹን አስመረቀ

ከሁለት ዓመት በፊት በዲጂታል ስልጠናዎች ዘርፍ የተሰማራው ካሊፎርኒያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በአጫጭር ስልጠናዎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡ ድርጅቱ ከሚጣቸው ስልጠናዎች መካከልም በዲጂታል ማርኬቲንግ፣ ዌብሳይት ማበልጸግ፣ ኮዲንግ፣ግራፊክ ዲዛይኒንግ እና ተዛማጅ ሙያዎች ዋነኞቹ ናቸው፡፡ መሰረታዊ የኮምፒዩተር እውቀት ካላቸው ፣ማህበራዊ ሚዲያዎችን መጠቀም የሚችሉ ሰዎች ማንኛውም ማንበብ እና መጻፍ የሚችሉ ሰዎች ስልጠናውን ማግኘት እንደሚችሉም የኢንስቲትዩቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሱራፌል አሰፋ በምረቃው ወቅት ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹ  ለአንድ ወር  ተኩል የተግባር ትምህርትን ጨምሮ  የተለያዩ መሰረታዊ ስልጠናዎችን አግኝተዋል።  ከተመራቂዎቹ  ውስጥ   ከግማሽ በላይ  ወንዶች ሲሆኑ  የዛሬ ተመራቂዎቹ   ሁለተኛ ዙር ተመራቂዎቹ ናቸው። በዲጂታል ማርኬቲንግ  ኢንተርኔትን በመጠቀም  በሞባይል ስልክ  ፣ በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችን፣ ዌብናሮችን፣ በሰርች ኤንጅ ሌሎች ዲጂታል መድረኮችን  በመጠቀም የዛሬ ተመራቂዎች ምርትና…
Read More
በአማራ ክልል የሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች በጦርነት ምክንያት ተማሪዎቻቸውን መጥራት አልቻሉም

በአማራ ክልል የሚገኙ 10 ዩንቨርሲቲዎች በጦርነት ምክንያት ተማሪዎቻቸውን መጥራት አልቻሉም

አማራ ክልል የሚገኙ አስር ዩኒቨርሲቲዎች በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለነባር እንዲሁም አዲስ ለተመደቡ ተማሪዎቻቸው ጥሪ ሳያደርጉ ወራት መቆጠሩ ይታወቃል፡፡ ከአማራ ክልል ውጪ የሚገኙ ዩንቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ጠርተው በማስተማር ላይ ሲሆኑ በአማራ ክልል ባሉ ዩንቨርስቲዎች የተመደቡ ተማሪዎች ግን እስካሁን አልተጠሩም። ይህንን ተከትሎም ተማሪዎቹ ለስነልቦና እና ለተለያዩ ችግሮች መጋለጣቸውን በተደጋጋሚ በማንሳት ላይ ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲዎቹ ጥሪ ሳያደርጉ አራት ወራት በማለፉ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መግባታቸውንም ይጠቁማሉ፡፡ "ያለ ትምህርት ቁጭ ብለን ወራት አልፈዋል፣ ፍትህ እንሻለን" የሚሉት ተማሪዎቹ፤ ወደ ሌሎች የትምህርት ተቋማት በጊዚያዊነት መዘዋወርን ጨምሮ አማራጭ መፍትሔዎች እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በበኩሉ በአማራ ክልል ያሉ ዩንቨርሲቲዎች በቅርቡ ለተማሪዎቻቸው ጥሪ እንዲያስተላልፉ መግባባት ላይ መደረሱን አስታውቋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር…
Read More