Blog

የቢል እና ሜሊንዳ ጌት ሥራ አስኪያጅ ማርክ ሱዝማን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

የቢል እና ሜሊንዳ ጌት ሥራ አስኪያጅ ማርክ ሱዝማን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው

የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ሥራ አስኪያጅ ማርክ ሱዝማን ከሚያዚያ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ መሆኑን አስታወቁ፡፡ ስራ አስኪያጁ ለአንድ ሳምንት በሚያደርጉት ጉብኝት በጤና ነክ ተግዳሮቶች ላይ ለመምከርና ለኢትዮጵያውያን ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን የሚቀርፉ እድሎችን ለማመቻቸት ይሠራሉ ተብሏል። ጉብኝቱ የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ከመሪዎችና ከማህበረሰቡ ጋር በቅርበት ሆኖ በመሥራት በመላው አፍሪካ ያሉ ዜጎችን ኑሮ መሻሻል የሚያፋጥኑ መፍትሔዎችን ለመደገፍ እያሳየ ያለው ቆራጥነት አካል ነው። በዚህ ጉብኝት ወቅት፤ ሱዝማን የመንግሥት ባለሥልጣናትን፣ ለጋሽ ድርጅቶችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖችን፣ የሳይንስ ሰዎችን፣ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን፣ በቦታው ተገኝተው የሚሠሩ የጤና ባለሙያዎችንና እና የፈጠራ ባለሙያዎችን ጨምሮ የተለያየ ዘርፍ ላይ ከሚገኙ ባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በነዚህ ውይይቶች ወቅት ሱዝማን አጋሮቻቸው…
Read More
በአፍሪካ በየአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየ ዓመቱ 250 ሺህ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ተገለጸ

በአፍሪካ በየአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በየ ዓመቱ 250 ሺህ ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ተገለጸ

የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ፍትህ ጥምረት ከዓለም ጤና ድርጅት ፣ አፍሪካ ጤና እና ጥናት ፋውንዴሽን፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና  ሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳቶች ዙሪያ በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ባለሙያዎች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና የተለያዩ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ የፓን አፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፍትህ ጥምረት ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሚቲካ ምዌንዳ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የአየር ንብረት ለውጥ ዜጎችን ለተደራራቢ የጤና ችግሮች እየዳረገ ነው ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ የሰው ልጆች ለአየር ወለድ፣ ውሃ ወለድ፣ ለምግብ እጥረት እና ሌሎች የጤና ችግሮች እየዳረገ ነው ያሉት ስራ አስፈጻሚው ጉዳቱን ለመቀነስ የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡…
Read More
ኢትዮጵያ ከዓለም ከአይኤምኤፍ ጋር ያላትን ልዩነት መፍታት እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከዓለም ከአይኤምኤፍ ጋር ያላትን ልዩነት መፍታት እንዳልቻለች ተገለጸ

የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በዋሸንግተን በተካሄደው የዓለም የገንዘብ ድርጅት ጉባኤ ላይ እየተካፈለች ትገኛለች፡፡ በዚህ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ እና የብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ ማሞ ምህረቱ እንዲሁም ሌሎች ባለስልጣናትም እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያ ከዓለም የገንዘብ ድርጅት 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት የጠየቀች ሲሆን ተቋሙ ግን ብድር ለኢትዮጵያ ከመስጠቱ በፊት የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጧል፡፡ ከተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል ኢትዮጵያ የብሯን የመግዛት አቅም እንድታዳክም የሚለው ሲሆን ይህ ጉዳይ እስካሁን አጨቃጫቂ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ኢትዮጵያ እና የዓለም ገንዘብ ድርጅት ድርድር ሲያደርጉ ከአንድ ዓመት በላይ የሆናቸው ሲሆን በየጊዜው ሳይስማሙ በመለያየት ላይ ናቸው፡፡ ከአንድ ወር በፊት የዓለም ገንዘብ ድርጅት ከፍተኛ ባለሙያዎች ወደ አዲ አበባ መጥተው…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

ከአላማጣ እና አካባቢው 29 ሺህ ህዝብ መፈናቀሉ ተገለጸ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 29 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ሰሜን ወሎ እና ሰቆጣ ከተማ በሚገኙ መጠለያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
በኢትዮጵያ 9 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ 9 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በፀጥታ ችግር ምክንያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 8.8 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። በኢትዮጵያ በግጭት ምክንያት 8,977 ትምህርት ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 6,483 ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆናቸውን በሚኒስቴሩ 'ትምህርትን በአደጋ ማስቀጠል' ባለሙያ ንጋቱ አበበ ተናግረዋል፡፡ ሚኒስቴሩ እና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በጋራ በመሆን የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል ጥረት ቢያደርጉም፤ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች በቀጠሉት ግጭቶች ምክንያት ችግሩን ለመፍታት አስቸጋሪ እንደሆነ ባለሙያው ጠቁመዋል፡፡ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉም ባለሙያው ጥሪ አቅርበዋል። ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት እየተካሄደ ባለበት የአማራ ክልል ውስጥ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን…
Read More
የባህር ሀይል ወታደሮች በአማራ ክልል ውጊያ እየተሳተፉ መሆኑን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ገለጸ

የባህር ሀይል ወታደሮች በአማራ ክልል ውጊያ እየተሳተፉ መሆኑን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ገለጸ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ እንዳለው "የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ማሪን ኮማንዶ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ተሰማርቷል" ብሏል። ተቋሙ የባህር ሀይል ዋና አዛዥ ተወካይ ሬር አድሚራል ናስር አባዲጋን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው "ጽንፈኛ" ባላቸው ቡድን አባላት ላይ እርምጃ እንደወሰደ ገልጿል። የኢትዮጵያ ባህር ሀይል ማሪን ኮማንዶዎች በሰሜን ሸዋ ዞን ባሉ ወረዳዎች እንደተሰማሩ እና ግዳጃቸውን እየተወጡ እንደሆነም አዛዡ መናገራቸው ተገልጿል። እንዲሁም ማሪን ኮማንዶ በመርከብ ላይ በባህር ከሚሰጠው ተልዕኮ በተጨማሪ በማንኛውም ጊዜ ግዳጁን የሚወጣ ሀይል እንደሆነም ሬር አድሚራል ናስር አባድጋ ተናግረዋል ተብሏል። ማሪን ኮማንዶ ከአማራ ክልል የጸጥታ ሀይሎች ጋር በመሆን በወሰዳቸው እርምጃዎች የክልሉ ሰላም እየተሻሻለ መምጣቱንም በዚሁ ዘገባ ላይ ተጠቅሷል። የፌደራል መንግሥት…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች አስታወቀች

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች አስታወቀች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ፣ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስለተደረገው የወደብ መግባቢያ ስምምነት እና ሌሎቹም ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ነብዩ እንዳሉት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ በድንበር አካባቢ ያሉ ማህበረሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መንገድ በሁለቱ ሀገራት በሚዋቀር ኮሚቴ ይፈታል ብለዋል። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ በኤርትራ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ድንበር ሊቀየር በማይችል ኹኔታ ለመጨረሻ ጊዜ ተሠምሯል ማለቱ አይዘነጋም። የኤርትራ ጦር በርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን እንደተቆጣጠር እና አካባቢዎቹን ወደ ኤርትራ ማካለሉን እንዴት ኢትዮጵያ እንዴት ታየዋለች? በሚል ለቃል አቀባዩ ለቀረበላቸው ጥያቄም "ጥያቄው…
Read More
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ3 ሺህ በላይ ህጻናት ከከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ ጋር እንደሚወለዱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ3 ሺህ በላይ ህጻናት ከከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ ጋር እንደሚወለዱ ተገለጸ

በዓለም አቀፍ ደረጃ የከንፈር እና ላንቃ ስንጥቃት ላጋጠማቸው ህጻናት ድጋፍ በማድረግ ዘርፍ የተሰማራው "ስማይል ትሬን" የተሰኘው ተቋም ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ መስራት ከጀመረ ከ20 በላይ ሆኖታል። ድርጅቱ ከሌላኛው ዓለም አቀፍ የጤና ተቋም ላይፍ ቦክስ ከተሰኘው ተቋም ጋር በመቀናጀት ደህንነቱ የተጠበቀ የቀዶ ህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። እነዚህ ሁለት ተቋማት ቲም ክሌፍት ከተሰኘ የሀገር በቀል ድርጅት ጋር በመቀናጀት የከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ ያጋጠማቸው ህጻናትን የቀዶ ጥገና ህክምና ለሚሰጡ የህክምና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል። ዶ/ር ቤቴል ሙልጌታ የስማይል ትሬን ምስራቅ አፍሪካ ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ ሲሆኑ እርሳቸው የሚመሩት ቢሮ በኢትዮጵያ ካሉ ከ20 በላይ የግል እና የመንግስት ሆስፒታሎች ጋር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ…
Read More
አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ለምን በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ላለው ጦርነት ትኩረት ነፈጉ?

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ለምን በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ላለው ጦርነት ትኩረት ነፈጉ?

በፌደራል መንግስት እና የትግራይ ታጣቂዎች መካከል የተካሄደው እና ለሁለት ዓመት የዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ መዲና ፕሪቶሪያ በተፈረመ የሰላም ስምምነት መቆሙ ይታወሳል፡፡ ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ጦርነት ተፋላሚዎች ወደ ተኩስ አቁም እንዲሄዱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት ቡድን ሰባት፣ ብሪታንያ እና ሌሎችም ተጽዕኖ ፈጣሪ ሀገራት በጋራ እና በተናጠል የተለያዩ ጫናዎችን ሲያደርጉ ነበር፡፡ ጦርነቱ በፍጥነት ባለመቆሙ ምክንያትም ሀገራት በኢትዮጵያ ያላቸውን ፕሮግራሞች ማቋረጥ፣ ቢሮ መዝጋት፣ እንደ አግዋ ኤነት ለኢትዮጵያ ተሰጥተው የነበሩ የገበያ እድሎችን መከልከል፣ ተፈቅደው የነበሩ ብድሮችን መከልከል  እና የቀጥታ በጀት ድጋፎችን ማቋረጥ በኢትዮጵያ ላይ ከተደረጉ ጫናዎች ዋነኞቹ ነበሩ፡፡…
Read More
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከአንድ ዓመት በኋላ ዳግም ተቀሰቀሰ

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከአንድ ዓመት በኋላ ዳግም ተቀሰቀሰ

የትግራይ ታጣቂዎች ወደ አማራ ክልል ዘልቀው ወረዳዎን እና ቀበሌዎችን በሀይል እንደተቆጣጠሩ ተገልጿል፡፡ የአማራ ክልል መንግስት ባወጣው መግለጫ ህወሓት በፕሪቶሪያ የተፈረመውን የዘላቂ የሰላም ስምምነት በመጣስ ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ፈጽሞብኛል ሲል ከሷል። በፌደራል መንግስት በኩል ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ውይይት ለማድረግ መጣሩን የገለጸው ክልሉ፣ ህወሓት የሰላም አማራጮችን ወደ ጎን በመተው በስምምነት አወዛጋቢ ተብለው የተለዩትን የራያ አላማጣ፣ የራያ ባላ፣ የኦፍላ፣ የኮረም እና ዛታ አካባቢዎችን ወርሯል ብሏል። የክልሉ መንግስት እንዳለው ህወሓት ለአራተኛ ዙር ወረራ በመፈጸም በህወሓት እና በፌደራል መንግስት መካከል ከተካሄዱት "ከባለፉት ሶስት ዙር ደም አፋሳሽ ጦርነቶች" አለመማሩን የሚያሳይ ነው። የአማራ ክልል ወረራ ተፈጽሞባቸዋል ያላቸው ቦታዎች እና የወልቃይት፣ ጠገዴ እና ጠለምት በ2013 ጦርነት ከመቀስቀሱ…
Read More