Oromia

በአማራ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ 300 ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ

በአማራ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ 300 ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ

የኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚዋሰኑበት የሰሜን ሸዋ ዞን ስራ የሚገኙ ወረዳዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ ደራ የተሰኘው ወረዳ ደግሞ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት የሚደርስበት አካባቢ ሲሆን በሶስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ 300 ንጹሃን ዜጎች በታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል፡፡ ኦነግ ሸኔ ከሶስት ዓመት በፊት  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ መንግስት ይህን የሽብር ቡድን ለማጥፋት እርምጃ እየወሰድኩ ነው ቢልም ቡድኑ ጥቃት ማድረሱን ቀጥሏል፡፡ አንድ ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የደራ ወረዳ ነዋሪ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ እንዳሉት "በሦስት ሳምንታ ውስጥ ከ300 በላይ ንጹሐን በሸኔ ታጣቂዎች ተገድለዋል።" ያሉ ሲሆን፤ ይህ እርሳቸው ያላቸው ትክክለኛ መረጃ እንደሆነ በመግለጽ፤ የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችል እርግጠኛ መሆናቸውን…
Read More
ኢትዮጵያ በእርዳታ ስርጭት ላለመሳተፍ መስማማቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በእርዳታ ስርጭት ላለመሳተፍ መስማማቷ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ካሳለፍነው ግንቦት ወር ጀምሮ የመጋዝን ስርቆት ተፈጽሞብናል በሚል እርዳታ መስጠት አቁመው ነበር፡፡ እርዳታ መቆሙን ተከትሎም ስደተኞች እና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ረሀብን ጨምሮ ተረጂዎች ህይወታቸውን እስከማጣት መድረሳቸው በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ በእርዳታ እህል ስርቆቱ ላይ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ባለስልጣናት እጃቸው እንዳለበት በወቅቱ በረድኤት ድርጅቶቹ በኩል ተገልጾም ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለተረጂዎች የተቀመጠን እህል ወደ ጎረቤት ሀገር ይላክ እንደነበርም የተገለጸ ሲሆን የፌደራል መንግስት በወቅቱ የቀረበበትን ክስ ውድቅ አድርጓል፡፡ የአሜሪካ የልማት ተራድዖ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ዛሬ ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ያቋረጠውን የምግብ እርዳታ ዳግም ለማስጀመር መወሰኑን አስታውቋል፡፡ እርዳታው የተጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት ከእርዳታው ጋር በተያያዘ በስርጭቱ ላይ እጁን እንደማያስገባ ከተስማማ በኋላ…
Read More
በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ የታሰሩ ሰዎች ህይወት በተስቦ በሽታ ማለፉ ተረጋገጠ

በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ የታሰሩ ሰዎች ህይወት በተስቦ በሽታ ማለፉ ተረጋገጠ

190 እስረኞች ታመው ህክምና ሲወስዱ ሶስት ሰዎች ደግሞ በጽኑ ህክምና ክትትል ውስጥ መሆነቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ወይም ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳድር ስር ባለ ሲዳሞ አዋሽ የታሰሩ ሰዎችን አስመልክቶ ያደረገውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል። ኮሚሽኑ ነሐሴ 24 እንዲሁም በጳጉሜን 2 እና 3 ቀን 2015 ዓ.ም. በዚህ ማቆያ ማእከል/ቦታ ባደረገው ጉብኝት እንዲሁም፣ በማቆያ ማእከሉ የሚገኙ ሰዎችን እና የአዲስ አበባ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮን ጨምሮ የሚመለከታቸውን የመንግሥት የጸጥታ አካላት በማነጋገር ክትትል አካሂጃለሁ ብሏል። በተጨማሪም የማቆያ ማእከሉ አስተባባሪዎች እና ጥበቃ ሲያደርጉ የነበሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላትን፣ በቦታው የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ የሕክምና ባለሞያዎችን እና ተጨማሪ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኝ የነበረውን የጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ኃላፊዎችን እና ባለሞያዎችን በማነጋገር…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ጠየቀች

ኢትዮጵያ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ግማሽ ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ገለጸች የቀድሞው ተዋጊዎችን የተሃድሶ ስልጠና ሰጥቶ ወደ ህብረተሰቡ ለመቀላቀል ከ554 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እንደሚያስፈልግ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩ ይህን የተናገሩት ኮሚሽኑ የቀድሞው ተዋጊዎችን መልሶ በዘላቂነት በማቋቋም ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ሚናና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ባካሄደው ውይይት ላይ ነው፡፡ የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ሃላፊ ገመዳ አለሚ በበኩላቸው ይህ  የገንዘብ መጠን በመነሻነት የታቀደ እንደነበረ የጠቀሱት ኮሚሽነሩ አሁን ላይ ግን ከተጠቀሰው ከፍ ማለቱን ተናግረዋል ። በኢትዮጵያ 372 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች እንዳሉ የተሀድሶ ማዕከል እና የሀገር መከላከያ ሚንስቴር በጋራ ያጠኑት ጥናት ያስረዳል። የተመዘገበው አሐዝ ይህ ቢሆንም ቁጥር ሊያሻቅብ…
Read More

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጦርነት 350 ሺህ ሰዎች መገደላቸውን ገለጸች

አሜሪካ ኢትዮጵያን ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገርነት ዝርዝር ውስጥ ሰርዛለች። በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ነበር አሜሪካ ኢትዮጵያን የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገር ዝርዝር ውስጥ የመዘገበቻት። ይህን ተከትሎም ዋሽንግተን ለኢትዮጵያ ታደርጋቸው የነበሩ የልማት ስራዎች ድጋፎችን አቋርጣ ቆይታለች። እንደ ፎሬይን ፖሊሲ ዘገባ ከሆነ አሜሪካ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጸምባት ሀገር አይደለችም የሚል አቋም ላይ ደርሳለች። በኮሮና ቫይረስ፣ በጦርነት እና በዓለም አቀፍ ንግድ መቀዛቀዝ ምክንያቶች ኢትዮጵያ እንደ ሌሎች ሀገራት የብድር መክፈያ ጊዜ ሽግሽግ እንዲደረግ አስቀድማ ጠይቃ ነበር። ይሁንና አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በጣለችው እገዳ ምክንያት ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ለብዙ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት ያደረጉትን የገንዘብ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ማድረግ…
Read More
በኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአንድ ዓመት ውስጥ ደግሞ ከ5 ሺህ በላይ ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰላም ጥናት ማዕከል አስታውቋል የኢትዮጵያ ፒስ ኢብዘርቫቶሪ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ሪፖርት መሰረት በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ኢትዮጵያዊያን ተገድለዋል ብሏል። ከሰኔ 3 ቀን እስከ 9 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ሰባት ቀናት ውስጥ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተፈጠሩ የፖለቲካ ግጭቶች ምክንያት 100 ሰዎች መገደላቸውን የግጭት ሁኔታ መረጃዎችን የሚያቀርበው “ኢትዮጵያ ፒስ ኦብዘርቫቶሪ” አስታውቋል። ዓለም አቀፍ የግጭት ሁኔታ እና የክስተት የመረጃ በመሰብሰብና በመተንተን የሚታወቀው “The Armed Conflict Location & Event Data Project” የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ይህንኑ ሥራ በኢትዮጵያ እንዲሠራ በፕሮጀክት ደረጃ ያቋቋመው፣ “Ethiopia Peace Observatory” የተባለው ተቋም ባወጣው ሳምታዊ ሪፖርት፤ በሳምንቱ ከተገደሉት 100…
Read More
በኦሮሚያ ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ከ50 በላይ ሰዎች ታገቱ

በኦሮሚያ ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ከ50 በላይ ሰዎች ታገቱ

በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የታገቱትን ሰዎች ለማስለቀቅ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ ባሳለፍነው ቅዳሜ ማለዳ ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር በመጓዝ ላይ የነበሩ ከ50 በላይ መንገደኞች ታይተዋል ። እገታውን የፈጸሙት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ናቸው የተባለ ሲሆን ለአንድ ሰው አንድ ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ የታጋች ቤተሰቦች ታጣቂዎቹ እየደወሉ መጠየቃቸው ተገልጿል። እገታው የተፈጸመበት ስፍራ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ሲሆን የፌደራል ፖሊስም ሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ታጣቂዎቹ በዜጎች ላይ እገታውን ሲፈጽሙ ማስጣል እንዳልቻለ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል ። በዚህ አካባቢ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች የሚያደርሱትን ጥቃት በመፍራት የሌሊት ጉዞ ከቆመ አንድ ዓመት እንዳለፈውም ነዋሪዎቹ…
Read More
የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ መምህራኑን ይዞ ሲጓዝ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 20 ደርሷል። ዛሬ ረፋድ የመደ ወላቡ መምህራንን ይዞ ሲጓዝ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር 20 መድረሱን ዩንቨርሲቲው አስታውቋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ዛሬ ማለዳ ለማስተማር ወደ ሻሸመኔ ካምፓስ በመጓዝ ላይ እያሉ የትራፊክ አደጋ ደርሶባቸዋል። መምህራኑን የጫነው ተሸከርካሪው መንገድ ስቶ ወደ ገደል በመግባቱ በተፈጠረው በዚህ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ ይገኛል። ከአደጋው በሕይወት የተረፉት ሌሎች ሰዎች በአደባ፣ ዶዶላ እና ሮቤ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢብራሂም…
Read More
የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የፌደራል መንግሥት እና ኦሮሚያ ነጻነት ሰራዊት ድርድር አለመሳካቱ ተገለጸ

የመንግስት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በማስወገድ ሰላምን ለማምጣት ያለመውና በታንዛኒያ ሲካሄድ የቆየው የሰላም ውይይት የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቋል ብሏል። ውይይቱ በአብዛኛው በአዎንታዊ መልኩ የተከናወነ ነው ያለው ሚንስቴሩ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ግን በዚህኛው የውይይት ምዕራፍ ስምምነት ላይ አልተደረሰም ብሏል። ግጭቱን በዘላቂነትና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለማስቆም እንዲቻል ሁለቱም አካላት የሰላም ውይይቱን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑ ላይ እንደተግባቡ ተገልጿል። በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና እስካሁን ሲመራባቸው በነበሩ መሠረታዊ መርሖች መሠረት ግጭቱን በሰላማዊ መልኩ ለመፍታት መንግስት የጸና አቋም እንዳለው በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል። ይህንን መልካም አጋጣሚና በውይይት ችግሮችን የመፍታት በጎ ጅምር በመጠቀም ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ የኢትዮጵያ መንግሥት ፅኑ አቋም እንዳለው አስታውቋል። አሜሪካ በታንዛኒያ ራስ…
Read More
መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር መረጃ እንዲሰጥ ተጠየቀ

መንግስት ከኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ጋር እየተደረገ ስላለው ድርድር መረጃ እንዲሰጥ ተጠየቀ

መንግሥት ‹‹ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት›› ጋር ስለሚያደርገው ድርድር በቂ መረጃ ይስጥ ሲል ኢዜማ አሳስቧል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መንግሥት ራሱን ‹‹የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት›› ከሚለው ታጣቂ ቡድን ጋር ስለሚያደርገው ድርድር በቂ መረጃ ይስጥ ሲል ጠይቋል፡፡  ፓርቲው በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኦሮሚያ ክልል በተደጋጋሚ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት ሲገደሉ ንብረታቸውም ሲወድምና ከቀያቸው ሲፈናቀሉ በግልጽ ተመልክተናል ብሏል፡፡ መንግስትም በተደጋጋሚ የተፈፀሙትን በደሎች ይህ ታጣቂ ቡድን ሲፈፅማቸው እንደነበር ከማሳወቁ አንፃር ይህን መሰል የዜጎች ሰቆቃ የሚያስቆም ድርድር ውስጥ መግባቱን ፓርቲው እንደሚደግፈው ገልጿል፡፡  ይሁንና ብልጽግና ኢትዮጵያን መምራት ከጀመረበትን ጊዜ ጨምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት በተለያየ ጊዜ የሚፈጸሙ ድርድሮች ግልጽነት የጎድላቸው እና አፈፃፀማቸው ደካማ መሆናቸውን ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡ ለአብነትም ከሕወሓት…
Read More