01
Mar
ግዙፉ የለንደኑ ዌምብሊ ስታድዬም 90 ደቂቃ ሞልቷል የሚል ምልክት ሲያሳይ የዩናይትድ ደጋፊዎች በኩራት ስካርፋቸውን ወደሰማይ ሰቅለው አውለበለቡ። ቀያዮቹ ሰይጣኖችና ደጋፊዎቻቸው ይህን ስሜት ካጣጣሙ ዓመታት ተቆጥረዋል። ደጋፊዎች ፊሽካው ከመነፋቱ በፊት ድላቸውን ሲያጣጥሙ፤ ይህን ለውጥ የሾፈረው ግለሰብ የአሠልጣኞች መቆሚያ ሥፍራ ላይ ሆኖ ሁኔታውን በጥሞና ይከታተላል። ዩናይትድ ለመጨረሻ ጊዜ ዋንጫ ያነሳው በ2017 የአውሮፓ ሊግ ፍፃሜ ነው። ዩናይትዶች ዋንጫውን እንዳነሱ አውቀውታል። የመጨረሻዎች ሽራፊ ደቂቃዎች ያስጨነቋቸው አይመስሉም። በመጀመሪያው አጋማሽ በስድስት ደቂቃዎች ልዩነት አከታትለው ያስቆጠሯቸው ሁለት ጎሎችን አስጠብቀው መውጣት ብቻ ነው የሚጠበቅባቸው። ምንም እንኳ በሁለተኛው አጋማሽ ኒውካስል ዩናይትድ ተነቃቅቶ ቢመጣም ኳስና መረብን ሊያገናኝ አልቻለም። ኤሪክ ቴን ሃግ በዩናይትድ መንደር ለውጥ እያመጣ ነው ብሎ በድፍረት መናገር ይቻላል።…