Business

ማንችስተር ሲቲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን አሸነፈ

ማንችስተር ሲቲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን አሸነፈ

አጓጊው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ ቀርቶታል። ማንችስተር ሲቲ ቀሪ ሁለት ጨዋታ እየቀረው የ2022/23 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን አሸንፏል። የዘንድሮውን ውድድር ሳይጠበቅ ለረጅም ወራት ሲመራ የቆየው አርሰናል ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ እርግጥ ሆኗል። አርሰናል በትናንትናው ዕለት ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረገውን ጨዋታ መሸነፉን ተከትሎ በፔፔ ጋርዲዮላ የሚሰለጥነው ማንችስተር ሲቲ ሁለት ጨዋታዎች እየቀሩት ዋንጫ መብላቱን አረጋግጧል። ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ለማለፍ የሚደረገው ትንቅንቅ እንደቀጠለ ሲሆን ሊቨርፑል በአስተንቪላ መሸነፉ የተሳትፎ ተስፋውን አክስሟል። ከቦርንማውዝ የተጫወተው ማንችስተር ዩናይትድ በካዝሚሮ ብቸኛ ጎል ማሸነፉን ተከትሎ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ተስፋውን የበለጠ አለምልሟል። ከፕሪሚየር ሊጉ ላለመውረድ እየተደረገ ያለው ትንቅንቅ የቀጠለ ሲሆን ሳውዛምፕተን ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱን አረጋግጧል። ሊድስ ዩናይትድ፣…
Read More
ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በፊት ያሻሻለችውን የኤክሳይስ ታክስ ህግን ዳግም ማሻሻያ አድርጋለች። በተቻቻለው ህግ ሙሰረት ከዚህ በፊት ከፍተኛ ግብር የተጣለባቸው ምርቶች ከፍተኛ የሚባል የግብር ቅናሽ ተደርጎባቸዋል። እንዲሁም ከዚህ በፊት ግብር ያልተጣለባቸው ምርቶች ላይ ጭማሪ ከተደረገባቸቅ ምርቶች መካከል የሞባይል አገልግሎቶች (ኢንተርኔት ፣ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክት)፣  የገመድ አልባ ስልክ አገልግሎት፣ የገመድም ሆነ ገመድ አልባ የኢንተርኔት አገልግሎቶች የ 5 በመቶ ግብር ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ግን የኤክሳይዝ ታክስ ማስከፈያ ዋጋቸው የቀነሰ ምርቶች ስኳር ለህክምና ከሚውለው በስተቀር የ10 በመቶ ቅናሽ እንደተደረገባቸው ተገልጿል፡፡ ማስቲካ ፣ቸኮሌት እና ጣፋጭ ከረሜላ ምርቶች ከዚህ በፊት 20 በመቶ የኤክሳይስ ታክስ ተጥሎባቸው የነበሩ ሲሆን አሁን የ10 በመቶ ቅናሽ ከተደረገባቸው  ምርቶች መካከል ናቸው፡፡…
Read More
በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴውድሮስ የተሰየመች ሮኬት ለኹለተኛ ጊዜ ማስወንጨፉ ይታወሳል። ዩንቨርሲቲው በከተማዋ አቅራቢ በሚገኘው የጉና ተራራ ላይ የህዋ ምርምር ማዕከል ለመገንባት እቅድ መያዙን ገልጿል። 154ኛውን የአፄ ቴዎድሮስ ዝክረ-ሰማዕት መታሰቢያ በዓል አስመልክቶ የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፍ በአካባቢያቸው ባለ ቁሳቁስ ከ 2 ኪ.ሜትር በላይ መወንጨፍ የቻለች ሮኬት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንድ ዓመት በፊት አስወንጭፏል። ዩንቨርሲቲው በዚህ ዓመትም በተሻለ መልኩ ማስወንጨፍ መቻላቸውን ዩንቨርሲቲው ገልጿል። የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር አዲሱ ወርቁ እንዳሉት በ2014 የተሰሩት ሮኬትና መድፍ  ዋና አላማ የአጼ ቴዎድሮስን የመቅደላ መድፍን ለመድገምና ኢትዮጽያ ውስጥ የተሳካለት ሮኬትና መድፍ መስራት መቻል እንደሆነ ተናግረዋል።  ሚያዚያ 2014 በሮኬት ሳይንስ ማዕከል አሞራ ገደል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተወነጨፈችው ሮኬት የት…
Read More
የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አሸነፉ

የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አሸነፉ

አቢሲኒያ ባንክ ለሶስት እንስቶች አንድ ሚሊዮን ብር ሸለመ ባንኩ "አሚን አዋርድ" በሚል የሰየመውን የሥራ ፈጠራ ውድድር አጠናቋል፡፡ ውድድሩ ካሳለፍነው ህዳር ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ በሥራ ፈጠራቸው ይዘት እና ችግር ፈቺነታቸው ለተመረጡ 5 ተወዳዳሪዎች የእውቅናና የሽልማት መርሐ-ግብር በአዳማ ከተማ ተካሂዷል፡፡ በውድድሩ ላይ ከ1ኛ - 5ኛ ለወጡ ተሳታፊዎች በአጠቃላይ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የተሸለሙ ሲሆን ከ6ተኛ እስከ 20ኛ ድረስ ለወጡ ተሳታፊዎችም የማበረታቻ ሽልማት መሰጠቱን አቢሲኒያ ባንክ ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ የአንደኝነት ደረጃን በማግኘት የ1,000,000 ብር ተሸላሚ የሆኑት በአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩ ሦስት እንስቶች አሸንፈዋል፡፡ እንስቶቹ ‹ግሪን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ማዳበሪያ› በሚል በጋራ ባቋቋሙት ድርጅት ስም አሸናፊ በመሆን ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል፡፡
Read More
ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ደርጅቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት ውስጥ 10 ሺህ ቤቶችን እንደሚገነባ አስታውቋል፡፡ ከ30 አመታት በላይ በመኖሪያ ቤት ግንባታ እና በኮንስትራክሽን ዘርፉ የተሰማራዉ ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለገበያ ማቅረቡን አስታዉቋል። የፍሊንትስቶን መስራችና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጸደቀ ይሁኔ እንደተናገሩት ከ20 ሺህ ብር ጀምሮ እስከ 2 ሚሊዮን ብር ድረስ ዋጋ ያላቸዉን አክሲዮኖች ለሽያጭ መቅረባቸዉን ተናግረዋል። የአንዱ አክሲዮን ዋጋም 1 ሺህ ብር መሆኑን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ከሚቀጥለው ሐምሌ ጀምሮ ሽያጩ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ባለ አክሲዮኖች ባላቸዉ የድርሻ መጠን ተሰልቶ አልያም በፍላጎታቸዉ ተጨማሪ ገንዘብ ከፍለዉ የቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት እድል መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡ በዋነኛነት አክሲዮን ሽያጩ ያስፈለገዉ ተጨማሪ ካፒታል ለማግኘት ፣ ድርጅቱን ከ አምስት ሰዎች የሽርክና ባለቤትነት…
Read More
የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ። ኢትዮጵያ ከአገር ውስጥ ባንኮች የተበደረችውን ሳይጨምር ከውጭ አበዳሪ ምንጮች ተበድራ ያልመለሰችው የዕዳ መጠን 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚንስቴር አስታውቋል። እንደ ሚኒስቴሩ ሪፖርት ከሆነ ኢትዮጵያ ካለባት 28 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ውስጥ 54 በመቶ የተገኘው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት ባንክ ነው፡፡ 46 በመቶው ደግሞ ከቻይና እና ከሌሎች ውጭ የግል አበዳሪ ተቋማት የተገኘ እንደሆነ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ባለባት ከፍተኛ የውጭ ዕዳ ብድር ምክንያትም በዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት ምደባ ከፍተኛ የዕዳ ጫና ያለባቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ ተመድባለች። በተያያዘ ዜና ኢትዮጵያ ከሶስት ዓመት በፊት የቡድን 20 አገሮች የዕዳ ጫናን ለማቅለል ባዘጋጁት የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሥርዓት ለመጠቀም…
Read More
ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የኮይካ ሃላፊ ሊ ቢዩንግህዋ ፈርመውታል። የገንዘብ ድጋፉ የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመን ይውላል የተባለ ሲሆን በተለይም የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነትን ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል። የወተት ምርታማነትን የሚያሳድገው ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት እንደሚተገበር የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሮጄክቱ በወተት ልማት እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን መደገፍ ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግም ተገልጿል። የተሻሻሉ የወተት ላሞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ፣ የወተት ምርታማነትን መጨመር፣ በማህበር የተደራጁ ወተት አቅራቢዎችን የገበያ እድሎችን ማስፋት፣ ተጨማሪ ሌሎች አሰራሮችን መዘርጋት የፕሮጀክቱ ዓላማ ነው ተብሏል።…
Read More
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰት የሁለት ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰት የሁለት ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለመሳብ አቅዳ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርቱ ላይ እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር አግኝታለች፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ እንዳሉት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ወደ አገር ውስጥ ለመሳብ ታቅዶ 2.67 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ የኮሚሽኑ አፈጻጸም የዕቅዱን 61 በመቶ ብቻ ያሳካ ሲሆን በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት፣ በኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ያለው አለመረጋጋት እንዲሁም በዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት ምክንያት ያጋጠመው የዓለም ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ለአፈጻጸሙ መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ተብሏል፡፡ ወደ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የቴሌኮም ኩባንያ አሁን ደግሞ ተጨማሪ ፈቃድ ማግኘቱን አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ባንኩ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድን ለሳፋሪ ኮም መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡ ይህም ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የውጭ አገር ኩባንያ እንደሚያደርገው የብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመለክታል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን አዲስ ሀላፊነት መስጠቱ ይታወሳል። አምባሳደር ሔኖክ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳዮች…
Read More
ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኢንቨስተሮች በሙስና ምክንያት ከሚሰሩባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለቀው እየወጡ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የበጀት ዓመቱን ዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ የምርት ዘርፎች የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኩባንያዎች ከመንግስት ተቋማት መሪዎች እና ባለሙያዎች በሚጠየቁ ክፍያ ምክንያት መማረራቸው ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ የኢንቨስትመንት ኮሚሽኑንን ሪፖርት በገመገመበት ወቅት እንደገለጸው በኦሮሚያ ክልል ዱከም ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ኢስተርን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያሉ ኩባንያዎች ቅሬታ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት በዚህ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባደረጉት ምልከታ ኢንቨስተሮች የሚጠይቋቸውን ከትንሽ እስከ ትልቅ አገልግሎቶች በገንዘብ እየገዙ ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም በፓርኩ ላይ የባለቤትነት ስሜት ባለመኖሩ ፓርኮች ውስጥ እየገቡ ዘረፋ እየተፈጸባቸው መሆኑን የምክር…
Read More