Business

የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር ባንኮች የምሽት አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደውን ህግ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር ባንኮች የምሽት አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደውን ህግ ተቃወመ

ባንኮች እስከ ምሽት 3፡30 ሰዓት ድረስ ክፍት እንዲሆኑ የሚያስገድደዉ ደንብ ከባንኮች አሰራር ጋር የማይጣጣም ነዉ ሲል የባንኮች ማህበር አስታወቀ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣው ባንኮች እስከ ምሽት 3:30 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ ከባንኮች አሠራር ጋር የማይጣጣም መሆኑን ማህበሩ ገልጿል፡፡ ባንኮች በዘመናዊ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አማካይነት የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን ለደንበኞቻቸው በቀላሉ ማቅረብ እየቻሉ በመሆኑ፣ የምሽት አገልግሎት አላስፈላጊና አግባብነት የሌለው መሆኑን የባንኮች ማህበር አስታዉቋል። የባንኮች ማህበር ዋና ጸሀፊ አቶ ደምሰው ሞገስ እንደሚገልጹት፣ደንበኞች በፖስ ወይም ኤቴኤም ማሽኖች፣ በተንቀሳቃሽ ስልክ የባንክ መተግበሪያዎችና በኢንተርኔት ባንኪንግ አማካይነት የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት ስለሚችሉ ባንኮች እስከ ምሽት ክፍት ሆነው መቆየት አለባቸዉ የሚለዉ አስገዳጅ መመሪያ ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ በተጨማሪም…
Read More
ኢትዮጵያ ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ መክፈል ልትጀምር ነው

ኢትዮጵያ ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ መክፈል ልትጀምር ነው

የሮያሊቲ ክፍያ ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ መክፈል ይጀመራል ተብሏል የሙዚቀኞች የሮያለቲ ክፍያ ከሀምሌ ወር ጀምሮ መክፈል እንደሚጀመር ተገልጿል። መገናኛ ብዙሀን ለሙዚቀኞች የሮያሊቲ ክፍያ እንዲከፍሉ የሚያስገደደው መመሪያ የፊታችን ሀምሌ 1ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል። የሮያሊቲ ክፍያ ረቂቅ መመሪያው የሚመለከታቸው አካላትን ባሳተፈ መንገድ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን  ህጉን ለማስፈጸም ስልጣን የተሰጠው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ቢበዛ ከአምስት ወር በኃላ ፀድቆ ወደ ስራ እንደሚገባ የባለስልጣኑ ዋና ዳሬክተር አቶ ወልዱ ይመሰል ተናግረዋል። በኢትዮጲያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን አማካኝነት የተሰናደው ይህ ውይይት፣ሙዚቀኞች፣ ፕሮዲውሰሮች፣ደራሲያን እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈውበታል። ውይይቱ በዋናነት በሙዚቀኞች ሮያሊቲ ክፍያ ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ የክፍያ ቀመር  ተዘጋጅቷል። የኢትዮጵያ የቅጅና ተዛማጅ…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ50 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ እንደሚያወጣ ገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ50 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ እንደሚያወጣ ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ የዶላር ጨረታ በየ15 ቀኑ በተከታታይ አወጣለሁም ብሏል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየሁለት ሳምንት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታ ማካሄድ እንደሚጀምር አስታወቀ። ጨረታዎቹ ለሚቀጥሉት በርካታ ወራት የሚካሄዱ ሲሆን፣ ዓላማውም የማዕከላዊ ባንኩን የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬ ስርዓት ግብን ለማሳካት ነው ብሏል። የማዕከላዊ ባንኩ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በታሪኩ ከፍተኛው እንደሆነ ገልጾ በተለይ ከቅርብ ወራት ወዲህ፣ በሀገሪቱ ውስጥ ብቸኛው የወርቅ ገዥ ለሆነው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የቀረበው የወርቅ መጠን ከፍተኛ መሆን የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት ከተገመተው በላይ እንዲጨምር እንዳደረገው ጠቁሟል። ከዚህ ከተጠበቀው በላይ ከሆነው የውጭ ምንዛሪ ግኝት አንጻር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቀጣይ ወራት በመደበኛነት በየሁለት ሳምንቱ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታዎችን ለማካሄድ መወሰኑን አሳውቋል።…
Read More
ኢሠማኮ መንግስት ለአደጋ ጊዜ በሚል ከተቀጣሪ ሰራተኞች ገንዘብ ለመሰብሰብ ማቀዱን ተቃወመ

ኢሠማኮ መንግስት ለአደጋ ጊዜ በሚል ከተቀጣሪ ሰራተኞች ገንዘብ ለመሰብሰብ ማቀዱን ተቃወመ

የመንግስት እና የግል ተቋማት ከሚሰጧቸው የተለያዩ አገልግሎቶች “ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” የሚሆን ገቢ እንዲሰበስቡ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ባሳለፍነው ሳምንት ለፓርላማ መቅረቡ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሠማኮ) መንግስት ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል ሳይወስን ገንዘብ ለመሰብሰብ አዲስ ረቂቅ ማስተዋወቁ ማንም አይጠይቀኝም ከሚል የመነጨ ነው ብሏል፡፡ መንግስት ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወስን በፓርላማ የፀደቀውን አዋጅ ሳያስተገብር ከሰራተኛው ላይ ገንዘብ ለመሰብሰብ አዲስ ረቂቅ ማስተዋወቁ ማንም አይጠይቀኝም ከሚል የመነጨ ነውም ብሏል። የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን እንደ አዲስ እንዲቋቋም የታሰበው የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ለተቀጣሪ ሰራተኞች ራሱን የቻለ አደጋ ነው ብሎታል። ከሳምንት በፊት በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጁ የቀረበው የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋትና ስራ…
Read More
የብሪታንያው ግሪን ሞሽን የመኪና ኪራይ ኩባንያ በኢትዮጵያ ስራ ጀመረ

የብሪታንያው ግሪን ሞሽን የመኪና ኪራይ ኩባንያ በኢትዮጵያ ስራ ጀመረ

ኢትዮዽያ የእንግሊዙን ግሪን ሞሽን የመኪና ኪራይ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ ወደ አዲስ አበባ መምጣቱ ተገልጿል። ዋና መስሪያ ቤቱን በእንግሊዝ ያደረገው ግሪን ሞሽን የመኪና ኪራይ አገልግሎት አቅራቢ ኢትዮጵያን  80ኛ መዳረሻው በማድረግ ስራ መጀመሩ ተሰምቷል። ግሪን ሞሽን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ያደረገው በመኪና ኪራይ ዘርፍ ላለፉት 10 ዓመታት ሲሰራ የቆየው ኤክሰለንት የመኪና ኪራይ ድርጅት ነው፡፡ ስራውን በአዲስ አበባ እውን ለማድረግ ሁለት ዓመት የፈጀ ድርድር ሲደረግ ቆይቷል ተብሏል፡፡ በተለይ ኢትዮጵያን ለመጎብኘት የሚመጡ ሰዎች ለስብሰባ ለመሳሰሉት ጉዳዮች አዲስ አበባን የሚረግጡ ተጓዦች በቆይታቸው የመኪና ኪራይ የሚያስፈልጋቸው ከሆነ ገና ከመምጣታቸው አስቀድሞ የመኪና አይነቱንም ክፍያውንም መፈፀም እንደሚችሉ ተናግሯል። ይህ በመሆኑም የሀገርን ገፅታ ከፍ ያደርጋል የውጭ ምንዛሪ ግኝትንም ለመፍጠር እድል…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ። ሲቢኢ ካፒታል አክሲዮን ኢንቨስትመንት ባንክ እና ወጋገን ካፒታል አክሲዮን ማህበር ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ያገኙት የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንኮች ሆነዋል። እነዚህ ባንኮች ራሳቸውን ችለው የተቋቋሙ የካፒታል ገበያ ስራ ብቻ የሚሰሩ የኢንቨስትመንት ባንኮች ናቸው የተባለ ሲሆን በተጨማሪም ለአምስት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጭዎች ፈቃድ ተሰጥቷል። ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች መካከልም ኢትዮ-ፊደሊቲ ሴኩሪቲስ አ.ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ (Securities Dealer) ፣ ኤች ኤስ ቲ ኢንቨስትመንት አድቫይዘሪ ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ፣ ኢኩዥን የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ መሆናቸው ተጠቁሟል። ፈቃድ የተሰጣቸው አገልግሎት ሰጪዎች…
Read More
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ከ15 ዓመት በፊት በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ግንባታው የተጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ በያዝነው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ላይ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩ ከህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ በሰጡበት ውቅት እንዳሉት ህዳሴ ግድብን ከ6 ወር በኋላ እንመርቃለን ብለዋል፡፡ መንግስት ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ መንግስት ጋር በተለይም ከደህንነት መስሪያ ቤት ጋር ህዳሴን በተመለከተ ውይይት አድርገናል የተለያዩ ሃሳቦችም በህዳሴ ግድብ ዙሪያ አቅርበናል ብለዋል፡፡ መንግስት በህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ ጋር ለመነጋገርና ለመወያየት ዝግጁ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል:: የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ 15 ዓመታት ሊሞሉት አንድ ሳምንት ብቻ ቀርቶታል።…
Read More
የአፍሪካ ወጣቶች ሮቦቲክስ ውድድር በአዲስ አበባ ተጀመረ

የአፍሪካ ወጣቶች ሮቦቲክስ ውድድር በአዲስ አበባ ተጀመረ

የአፍሪካ ወጣቶች የሮቦቲክስ ፈጠራ ችሎታቸውን የሚያሳዩበት 3ኛው የአፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮንሺፕ ውድድር ዛሬ በታላቅ ድምቀት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ተጀምሯል። የኢትዮ ሮቦቲክስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰናይክረም መኮንን ለሦስት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ የመጀመሪያ ደረጃ፣ የሁለተኛ ደረጃ፣ የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በፈጠራ ችሎታቸው ይወዳደራሉ፤ ውድድሩም በዲዛይን፣ በኢንጂነሪንግ እና በአውቶኖሚ ኮዲንግ ላይ እንደሚያተኩር በመርሃግብሩ ማስጀመሪያ ላይ አስረድተዋል። አቶ ሰናይክረም የውድድሩ ዓላማ ወጣቶች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን ክህሎት ማዳበርና ማበረታታት እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግ ነው። በዚህ ውድድር አሸናፊ የሚሆኑ ተማሪዎች የዋንጫ ሽልማት እና ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተፈረመ የምስክር ወረቀት እንደሚያገኙ አስታውቀዋል። ለፍጻሜ የሚበቁ ተማሪዎች አገራቸውን ወክለው በአሜሪካ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የሮቦቲክስ…
Read More
የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ያላመኑበትን ግብር በጫና እንዲከፍሉ መደረጋቸውን ተናግሩ

የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ያላመኑበትን ግብር በጫና እንዲከፍሉ መደረጋቸውን ተናግሩ

የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ያላመኑበትን ግብርና ታክስ በተጨማሪ በሌሎች ችግሮች እየተፈተኑ እንደሚገኙ ተገለፀ የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ፎረም በከተማው ውስጥ የሚገኙ ባለሀብቶች ከባድ ችግሮች እያጋጠሟቸው መሆኑን ገልጿል። ፎረሙ የባለሀብቶችን ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል። የባለአብቶች ፕሬዝዳንት አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ለካፒታል እንደገለጹት፣ ባለሀብቶቹ ያላግባብ ድርጅቶቻቸው መታሸግ፣ መፍረስ፣ መነጠቅ (መቀማት)፣ ሥራ እንዲያቆሙ መደረግ፣ ያላመኑበትን ከፍተኛ ግብርና ታክስ ለማስከፈል ማስገደድ፣ የባንክ አካውንታቸው መታገድ፣ ከሀገር እንዳይወጡ ወይም እንዳይገቡ እየተደረጉ ነው ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ በስልክ ዛቻና ማስፈራሪያ ማድረስ፣ የማያምኑበትን አሰልቺና ተደጋጋሚ መዋጮዎች መጠየቅ፣ እንዲሁም ተረጋግተው ሥራቸውን እንዳይከውኑ ማዋከብ፣ የብድር አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ያለማግኘት እና የመሳሰሉት ችግሮች እየደረሱባቸው መሆኑን ሰምተናል ብለዋል። ይህን ተከትሎ ፎረሙ…
Read More
ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን ሳተላይት በ2026 ልታመጥቅ ነው ተባለ

ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን ሳተላይት በ2026 ልታመጥቅ ነው ተባለ

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂስፓሻል ኢኒስቲትዩት እንደገለጸው በፈረንጆቹ 2026 ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማምጠቅ በሥራ ላይ መሆኑን ገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ ቀጣይ ዓመት ለሶስተኛ ጊዜ ታመጥቃታለች የተባለው ሶስተኛ ሳተላይት ከዚህ ቀደም መጥቀው አገልግሎት ጊዜያቸው ካበቁት ሁለት ሳታላይቶች የተሻለ የምስል ጥራት ይኖራታል ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማምጠቅ ከቻይና መንግስት ጋር ተፈራርማ እየሰራች መሆኑን የነገሩን በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት የሳተላይት ክትትል ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ተስፋዬ ፉፋ ናቸው፡፡ አቶ ተስፋዬ ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን እና የተሻለ የመሬት ምልከታ ጥራት ያላትን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማምጠቅ ስራ መጀመሯን አስረድተዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ለማልማት በምን ያክል ገንዘብ ከቻይና ጋር…
Read More