መነሻ ገፅ

ራስ ገዞቹ ሶማሊላንድ እና ፑንትላንድ ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ ተናገሩ

ራስ ገዞቹ ሶማሊላንድ እና ፑንትላንድ ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ ተናገሩ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከአራት ወራት በፊት በወደብ ጉዳይ በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት እንድትሆን ሶማሊላንድ ደግሞ የሀገርነት እውቅና እንድታገኝ የሚያደርግ በመሆኑ ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣንና እና ተቃውሞን አስከትሏል። ከትናንት በስቲያም ሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደርን በ72 ሰዓት ውስጥ ሞቃዲሾን ለቃ እንድትወጣ እና በሀርጌሳ እና ጋሮዌ ያሉ የኮንሱላ ጽህፈት ቤቶች እንዲዘጉ ሰራተኞቹም በሁለት ሳምንት ውስጥ ሶማሊያን ለቀው እንዲወጡ መወሰኗን አስታውቃለች፡፡ ራስ ገዟ ሶማላንድ እና ፑንት ላንድ የሶማሊያ መንግስት በሀርጌሳ እና ጋሮዌ የሚገኙ ቆንስላዎች እንዲዘጉ ያሳለፈውን ውሳኔ መቃወማቸው ተነግሯል። ይህንን ተከትሎም ሶማሊያ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

ኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ የ1 ነጥብ 72 ቢሊዮን ዶላር ወይም የ97 ቢሊዮን ብር እርዳታ እና በድር ስምምነት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ተወካይ የሆኑት ኦስማን ዲዮን ተፈራርመዋል ተብሏል፡፡ ከዓለም ባንክ ከተገኘው የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ 850 ሚሊዮን ዶላር ያህሉ በእርዳታ ለኢትዮጵያ የተለያዩ ስራዎችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ቀሪው ገንዘብ ደግሞ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት እና ለማከናወን በሚል በብድር መልኩ ከባንኩ እንደተሰጠ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ በእርዳታ ከተሰጠው ገንዘብ ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላሩ ለገጠር አካባቢዎች የምግብ ዋስትና፣ የአየር ንብረት ለውጥ ስራዎችን ለመደገፍ፣ 82 ዶላሩ ደግሞ በከተማ አካባቢዎች ምግብ ዋስትና ስራዎችን ለማረጋገጥ…
Read More
የኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ ዉይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ ዉይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት እና ሀገራት ጋር እያደረገችው ያለው ውይይት አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋሙ አይኤምኤፍ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይቶችን ከሚያደርጉ አበዳሪ ተቋማት መካከል ዋነኛው ሲሆን ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ቆይታ አድርጎ መመለሱ ተገልጿል፡፡ አይኤምኤፍ በድረገጹ ባወጣው መረጃ በኢትዮጵያ መንግስት ጥያቄ መሰረት ከመጋቢት 10 እስከ 24 ቀን 2016 ዓም ድረስ በአዲስ አበባ ቆይታ አድርጎ ተመልሷል፡፡ ኢትዮጵያ ልታካሂደው ባሰበችው የኢኮኖሚ ሪፎርም ላይ አይኤምኤፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥያቄ እንዳቀረበች የገለጸው ይሄው ተቋም በአልቫሮ ፒሪስ የተመራ የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ቡድን ወደ አዲ አበባ መምጣቱን አስታውቋል፡፡ ለ15 ቀናት በዘለቀው በዚህ የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ ባለሙያዎች እና ባለስልጣናት መካከል የተደረገው ውይይት ገንቢ እንደነበርም ተገልጿል፡፡…
Read More
መንግስት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን መቆጣጠር የሚያስችለውን ህግ አወጣ

መንግስት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን መቆጣጠር የሚያስችለውን ህግ አወጣ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን አጽድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ አጽድቋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ተስፋዬ በልጂጌ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ መንገግስት የዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት የሆነውን የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ለማሻሻል የተለያዩ ጥረቶች እያደረገ ቢሆንም፤ ከመኖሪያ ቤት ፍላጎት ጋር ሊጣጣም አልቻለም ብለዋል። አቶ ተስፋዬ አክለውም ፤ በኢትዮጵያ የተጋነኑ እና ከተከራዮች የመክፈል አቅም በላይ የሆነ የቤት ኪራይ ጭማሪዎች በከተሞች እንዳሉ ተናገረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ በተለይ በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ እና ዜጎችም ተረጋግተው ኑሯቸውን…
Read More
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ አብዛኞቹ ቦታዎች ቀጣዮቹ ቀናት የበልግ ዝናብ በአብዛኛዎቹ የበልግ አብቃይ አካባቢዎች ላይ ይጠናከራል ተብሏል፡፡ በመጪዎቹ 10 ቀናት የበልግ ዝናብ በአብዛኛዎቹ የበልግ አብቃይ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ እየተጠናከረና እየተስፋፋ እንደሚሄድ የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል። ይህን ተከትሎም በበልግ አብቃይ አካባቢዎች በርካታ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል። በተጨማሪም በውሃ አካላትና በከባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዮሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት ምስራቅ ሸዋ፣ አዲስ አበባ፣ ምስራቅ አማራ፣ ሐረር፣ ድሬዳዋ እና አይሻ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ጠቅሷል። ከኦሮሚያ ክልል የቄለም ወለጋ፣ የምዕራብ ወለጋ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉአባቦር፣ ጅማ፣ ሁሉም የሸዋ ዞኖች፣ አርሲና ምዕራብ አርሲ፣ ባሌና ምስራቅ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ እንደምታነሳ ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ እንደምታነሳ ገለጸች

ኢትዮጵያ የየነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ሀገራት በመግዛት የምትሸፍን ሲሆን የትራንስፖርት ዋጋ እንዳያንር በሚል የነዳጅ ድጎማ ስታደርግ ቆይታለች፡፡ የመንግስት ወጪ በመጨመሩ እና የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ እና ለማቆም እንደወሰነች የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባሳለፍነው ዓመት ይፋ አድርጓል፡፡ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለማይሰጡ ድርጅቶች የነዳጅ ድጎማው ከቆመ አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን አሁን ደግሞ የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችም የነዳጅ ድጎማ እንደማያገኙ ተገልጿል፡፡ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ ሲደረግላቸው የነበሩ የሚኒባስ ተሽከርካሪዎች ከመጋቢት 30 ቀን  2016 ዓ.ም ጀምሮ ድጎማው እንደሚቋረጥ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል። መንግሥት ለረጅም ጊዜ ለነዳጅ ምርቶች ከፍተኛ መጠን የለው ድጎማን ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጽ ይህንን ለማስቀረት በሂደት የነዳጅ ምርቶች…
Read More
የአዲስ አበባ እምብርት ከምትባለው ፒያሳ 11 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን ከንቲባ አዳነች ተናገሩ

የአዲስ አበባ እምብርት ከምትባለው ፒያሳ 11 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን ከንቲባ አዳነች ተናገሩ

በአዲስ አበባ ከፒያሳ እና አካባቢው ከሳምንታት በፊት በተጀመረው የከተማ ማስዋብ ግንባታ ምክንያት 11 ሺህ ሰዎች መነሳታቸውን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል። ከንቲባዋ በሁሉም የመንግስት ሚዲያዎች በተላለፈ ንግግራቸው ላይ እንዳሉት “በድምሩ ወደ 11 ሺህ ሰው ይሆናል ከዚያ አካባቢ ወደተሻለ ቦታ የወሰድነው” ብለዋል። ነዋሪዎቹ መኖሪያ ቤታቸው የፈረሰው በፒያሳ አካባቢ ካሉት ራስ መኮንን ድልድይ፣ ማህሙድ ሙዚቃ ቤት፣ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ፣ አራት ኪሎ የሚገኘው አብርሆት ቤተ መጽሐፍት፣ ቴዎድሮስ አደባባይ እስከ ቸርችል ጎዳና ድረስ በሚያካልለው “የኮሪደር ልማት” ምክንያት የተነሱ ናቸው። ይህ የኮሪደር ልማት ከፒያሳ እስከ አራት ኪሎ ባለው አካባቢ የሚገኝ ሲሆን፣ 8.1 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍንም ከንቲባዋ ገልጸዋል። አዳነች በዚህ ሪፖርት ላይ ከተነሺዎቹ…
Read More
በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

የፍትህ ሚኒስቴር በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ ባሉ 52 ተጠርጣሪዎች ላይ የፖለቲካ ርዕዮትን በሀይል ለማስፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀል ህግ እንዲሁም የሽብር ወንጀሎችን ለመከላከል የወጣውን ህግ ጥሰዋል በሚል ክስ መስርቷል፡፡ በዚህ ክስ መዝገብ ስርም ክርስቲያን ታደለ፣ ዮሀንስ ቧያለው፣ ካሳ ተሸገር (ዶ/ር) ጫኔ ከበደ፣ እስክንድር ነጋ፣ ዘመነ ካሴ፣ አበበ ፈንታው፣ አሰግድ መኮንን፣ መከታው ማሞ፣ ፈንታሁን ሙሃባ እና ሌሎችም ተካተዋል፡፡ ከ52ቱ ተከሳሾች መካከል 14ቱ ተጠርጣሪዎች ልደታ በሚገኘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀሎች ችሎት የቀረቡ ሲሆን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ እና ቤተሰቦች መገኘታቸው ተገልጿል፡፡ የተጠርጣሪዎች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአልዐይን እንዳሉት በችሎቱ መገኘታቸውን ገልጸው ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ማንነት ካረጋገጠ በኋላ የተለያዩ ትዕዛዞችን…
Read More
መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን ለተመልካቾቹ አቀረበ

መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን ለተመልካቾቹ አቀረበ

ከመልቲቾይዝ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የሆነው ዲኤስቲቪ ለኢትዮጵያ ተመልካቾች የተለያዩ መዝናኛ ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ድርጅቱ በትናንትናው ዕለት ባዘጋጀው ፕሮግራም ከዚህ በፊት የነበሩ እና በቀጣይ ስለሚጀመሩ አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራሞቹን አስተዋውቋል፡፡ በመድረኩ ላይ አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ተጽዕኖፈጣሪ ሰዎች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የመልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ቁጥጥር እና ኮርፖሬት ሃላፊ አቶ መታሰቢያ በላይነህ በመድረኩ ላይ እንዳሉት መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ለደንበኞቹ በየጊዜው አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራም እና ይዘቶችን ያቀርባል ብለዋል፡፡ ድርጅቱ በዚህ ወቅት እንዳለው ከዚህ በፊት ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ሲያቀርባቸው ከነበሩት የመዝናኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪ አዳዲስ ይዘቶችን እንደሚያቀርብ ገልጿል፡፡ በድርጅቱ በኩል ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ይቀርቡ ከነበሩት ይዘቶች በተጨማሪ አዳዲስ ፕሮግራሞችን በአማርኛ እና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች የሚተላለፉ ይዘቶች…
Read More
ኢትዮጵያ ከማዕድን ንግድ ከ252 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘሁ አለች

ኢትዮጵያ ከማዕድን ንግድ ከ252 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘሁ አለች

በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ስምንት ወራት ከማዕድን ዘርፍ 252 ነጥብ 15 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል። የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማትዮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳሉት፤ በ2016 በጀት ዓመት የተለያዩ ዓይነት ማዕድናት ወደ ውጭ ገበያ በመላክ 252 ነጥብ 15 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። ባለፉት ስምንት ወራት ከሁለት ሺህ 673 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ፣ 66 ቶን በላይ ታንታለም እና ከ11 ሺህ 176 ቶን በላይ ሉቲየም ኦር ለውጭ ገበያ መቅረባቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም ከ99 ሺህ 021 በላይ ቶን የጌጣጌጥ እንዲሁም 29 ሺህ 281 ቶን በላይ የኢንዱስትሪ ማዕድናት ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉን አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል። የተገኘው ገቢ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት…
Read More