መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

የቻይናዋ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሼንዘን ከተማ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድርን ከግንቦት 16 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ታስተናግዳለች፡፡ በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች ወደ ቻይና ያቀኑ ሲሆን ለተወዳዳሪዎቹ የአሸኛኘት ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡ ውድድሩን ህዋዌ ያዘጋጀው ሲሆን በየሀገሩ በተካሄደ የማጣሪያ ውድድሮች ላይ አሸናፊ የሆኑ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ ተማሪዎቹ በዚህ  ዓለም አቅፍ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ያቀኑት የተለያዩ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ላይ ተሳትፈው በየደረጃው በአሸናፊነት በማጠናቀቃቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያን በዚህ ውድድር ላይ የወከሉት ዘጠኙ ተማሪዎች  የተገኙት ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች ነው። በውድድሩ ተማሪዎቹ  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን…
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዘጠኝ ኤጲስ ቆጰሳት እንዲሾሙ ወሰነች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዘጠኝ ኤጲስ ቆጰሳት እንዲሾሙ ወሰነች

ላለፉት አምስት ቀናት በደዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠናቋል። በጉባኤው የማጠቃለያ ፕሮግራም ችግር ባለባቸው እና አስፈላጊ በሆኑባቸው አህጉረ ስብከት 9 አዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ  ውሳኔ አሳልፏል። የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል። አቡነ ጴጥሮስ አክለውም "የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በሰላም እና ደስ በሚል ሁኔታ ተጠናቋል፣ ዛሬ የመጨረሻው አጀንዳ ላይ ብዙ ውይይት ተካሂዷል፣ በመጨረሻ ሁሉም አባቶች ተወያይተው ቤተክርስቲያንን የሚጠቅመው ምንድነው ? የሚለው ላይ በመምከር ውሳኔ ተላልፏል" ብለዋል። "የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት እንዲካሄድ ተወስኗል። የመጀመሪያው ችግር ያለባቸው ሀገረ ስብከት የሚል ሲሆን ይህንን የሚያስፈጽምም 7 አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሟል…
Read More
በቀን 35 ሺህ ብር ይቆጥቡ የነበሩ የሿሿ ሌቦች ተያዙ

በቀን 35 ሺህ ብር ይቆጥቡ የነበሩ የሿሿ ሌቦች ተያዙ

በአዲስ አበባ የ"ሿሿ " ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በተለምዶ "ሿሿ "የሚባለውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 25 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል። ወንጀል ፈፃሚዎቹ ኃይል በመጠቀም ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አንበሳ ጋራዥ አካባቢ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ኦሮ 86853 ነጭ ሚኒባስ በመጠቀም ከአንድ ግለሰብ ላይ 10ሺ ብርና ግምቱ 14 ሺብር የሚያወጣ ሞባይል ስልክ ሰርቀው ይሰወራሉ፡፡ ፖሊስ ጠንካራ  ክትትል  በማድረግ ወንጀል ፈፃሚዎቹን ከነተሽከርካሪው በቁጥጥር ስር በማዋልና ምርመራ በማስፋት ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት የሚፈፅሙ 14 ወንጀል ፈፃሚዎችንና  የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 ኦሮ 79184 ሚኒባስ ተሽከርካሪን…
Read More
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት 28 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ማድረሱ ተገለጸ

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት 28 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ማድረሱ ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም ማዕከሉን በትግራይ ክልል አድርጎ ለሁለት ዓመታት በተካሄደውና በሌሎች የተወሰኑ አካባቢዎች በነበረው ጦርነት፣ ከ1.5 ትሪሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳትና ኪሳራ በአገር ላይ መድረሱን ገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አደረገ። የገንዘብ ሚኒስቴርን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ተቋማቸው በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተካሄደው ጦርነት የደረሰውን ጉዳትና የመልሶ ግንባታ ፍላጎት የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት (Damage and Needs Assessment) ማከናወኑን ገልጸዋል ። በጥናት ግኝቱ መሠረትም ያጋጠመው አጠቃላይ ጉዳትና የኢኮኖሚ ኪሳራ በአጠቃላይ 28 ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን ተገልጿል። ለምክር ቤቱ በቀረበው ሪፖርት ላይ ከተቀመጠው መረጃ መረዳት እንደተቻለው፣ ‹‹22 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) 20.4…
Read More
ማንችስተር ሲቲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን አሸነፈ

ማንችስተር ሲቲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን አሸነፈ

አጓጊው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ ቀርቶታል። ማንችስተር ሲቲ ቀሪ ሁለት ጨዋታ እየቀረው የ2022/23 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን አሸንፏል። የዘንድሮውን ውድድር ሳይጠበቅ ለረጅም ወራት ሲመራ የቆየው አርሰናል ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ እርግጥ ሆኗል። አርሰናል በትናንትናው ዕለት ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረገውን ጨዋታ መሸነፉን ተከትሎ በፔፔ ጋርዲዮላ የሚሰለጥነው ማንችስተር ሲቲ ሁለት ጨዋታዎች እየቀሩት ዋንጫ መብላቱን አረጋግጧል። ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ለማለፍ የሚደረገው ትንቅንቅ እንደቀጠለ ሲሆን ሊቨርፑል በአስተንቪላ መሸነፉ የተሳትፎ ተስፋውን አክስሟል። ከቦርንማውዝ የተጫወተው ማንችስተር ዩናይትድ በካዝሚሮ ብቸኛ ጎል ማሸነፉን ተከትሎ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ተስፋውን የበለጠ አለምልሟል። ከፕሪሚየር ሊጉ ላለመውረድ እየተደረገ ያለው ትንቅንቅ የቀጠለ ሲሆን ሳውዛምፕተን ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱን አረጋግጧል። ሊድስ ዩናይትድ፣…
Read More
የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ መምህራኑን ይዞ ሲጓዝ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 20 ደርሷል። ዛሬ ረፋድ የመደ ወላቡ መምህራንን ይዞ ሲጓዝ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር 20 መድረሱን ዩንቨርሲቲው አስታውቋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ዛሬ ማለዳ ለማስተማር ወደ ሻሸመኔ ካምፓስ በመጓዝ ላይ እያሉ የትራፊክ አደጋ ደርሶባቸዋል። መምህራኑን የጫነው ተሸከርካሪው መንገድ ስቶ ወደ ገደል በመግባቱ በተፈጠረው በዚህ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ ይገኛል። ከአደጋው በሕይወት የተረፉት ሌሎች ሰዎች በአደባ፣ ዶዶላ እና ሮቤ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢብራሂም…
Read More
ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በፊት ያሻሻለችውን የኤክሳይስ ታክስ ህግን ዳግም ማሻሻያ አድርጋለች። በተቻቻለው ህግ ሙሰረት ከዚህ በፊት ከፍተኛ ግብር የተጣለባቸው ምርቶች ከፍተኛ የሚባል የግብር ቅናሽ ተደርጎባቸዋል። እንዲሁም ከዚህ በፊት ግብር ያልተጣለባቸው ምርቶች ላይ ጭማሪ ከተደረገባቸቅ ምርቶች መካከል የሞባይል አገልግሎቶች (ኢንተርኔት ፣ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክት)፣  የገመድ አልባ ስልክ አገልግሎት፣ የገመድም ሆነ ገመድ አልባ የኢንተርኔት አገልግሎቶች የ 5 በመቶ ግብር ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ግን የኤክሳይዝ ታክስ ማስከፈያ ዋጋቸው የቀነሰ ምርቶች ስኳር ለህክምና ከሚውለው በስተቀር የ10 በመቶ ቅናሽ እንደተደረገባቸው ተገልጿል፡፡ ማስቲካ ፣ቸኮሌት እና ጣፋጭ ከረሜላ ምርቶች ከዚህ በፊት 20 በመቶ የኤክሳይስ ታክስ ተጥሎባቸው የነበሩ ሲሆን አሁን የ10 በመቶ ቅናሽ ከተደረገባቸው  ምርቶች መካከል ናቸው፡፡…
Read More
በሸገር ከተማ አስተዳድር ከ10 በላይ መስጅዶች መፍረሳቸው ተገለጸ

በሸገር ከተማ አስተዳድር ከ10 በላይ መስጅዶች መፍረሳቸው ተገለጸ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በጉዳዩ ዙሪያ ጣልቃ እንዲገቡ  ተጠይቀዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በቅርቡ በአዲስ አበባ ዙሪያ "ሸገር ከተማ" ተብሎ በተመሠረተው ከተማ መስጅዶች እየፈረሱ መሆናቸውን ገልጿል። የመስጂድ ፈረሳው መቀጠሉን ተከትሎም  "አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጠው" የሚጠይቅ ደብዳቤ ምክር ቤዩ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጽፏል። ምክር ቤቱ በደብዳቤው፤ በከተማ አስተዳደሩ "ህገወጥ" በሚል በርካታ መስጂዶች እየፈረሱበት እንደሚገኙና፣ በጉዳዩ ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጋር በስልክ በመነጋገር መፍትሄ ላይ ደርሶ እንደነበር ገልጿል። ነገር ግን "የከተማ አስተዳደሩ በረመዳን ወር ለጊዜው የመስጂድ ፈረሳውን እንዲቆም በማድረግ ከረመዳን በኋላ የመስጅዶች ፈረሳ በአዲስ መልከ በብዛት ቀጥሏል"  ብሏል። ምክር ቤቱ በመግለጫው የመስጅድ ፈረሳ ጉዳይ በከተማ አስተዳደሩ "ህገ ወጥ" ስለተባለ…
Read More
ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲዋን ከማለዘብ ወደ ማሳመን መቀየሩን ገለጸች

ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲዋን ከማለዘብ ወደ ማሳመን መቀየሩን ገለጸች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በሰሜኑ ጦርነት ውስጥ በነበረችበት ወቅት  የደረሱ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ለመቋቋም "የማለዘብ ዲፕሎማሲ" ስትከተል መቆየቷን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ እና ተጨማሪ የዲፕሎማሲ ስራዎች በመሰራታቸው ይደርሱ የነበሩ ጫናዎች መቀነሳቸውን ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከማለዘብ ዲፕሎማሲ ወደ ማሳመን ዲፕሎማሲ መመለሷን የተናገሩት አምባሳደር መለስ የተለያዩ የዓለማችን ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻሻል መሪዎቻቸውን ወደ አዲስ አበባ በመላክ ላይ መሆናቸውን አክለዋል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ ከተማም ከኒዮርክ እና ጀኔቫ በመቀጠል ሶስተኛዋ የዓለማችን የዲፕሎማሲ ከተማ ይዞታዋ መመለሷን ቃል…
Read More
በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴውድሮስ የተሰየመች ሮኬት ለኹለተኛ ጊዜ ማስወንጨፉ ይታወሳል። ዩንቨርሲቲው በከተማዋ አቅራቢ በሚገኘው የጉና ተራራ ላይ የህዋ ምርምር ማዕከል ለመገንባት እቅድ መያዙን ገልጿል። 154ኛውን የአፄ ቴዎድሮስ ዝክረ-ሰማዕት መታሰቢያ በዓል አስመልክቶ የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፍ በአካባቢያቸው ባለ ቁሳቁስ ከ 2 ኪ.ሜትር በላይ መወንጨፍ የቻለች ሮኬት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንድ ዓመት በፊት አስወንጭፏል። ዩንቨርሲቲው በዚህ ዓመትም በተሻለ መልኩ ማስወንጨፍ መቻላቸውን ዩንቨርሲቲው ገልጿል። የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር አዲሱ ወርቁ እንዳሉት በ2014 የተሰሩት ሮኬትና መድፍ  ዋና አላማ የአጼ ቴዎድሮስን የመቅደላ መድፍን ለመድገምና ኢትዮጽያ ውስጥ የተሳካለት ሮኬትና መድፍ መስራት መቻል እንደሆነ ተናግረዋል።  ሚያዚያ 2014 በሮኬት ሳይንስ ማዕከል አሞራ ገደል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተወነጨፈችው ሮኬት የት…
Read More