መነሻ ገፅ

በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበትና በንፁኃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዲቆም አሜሪካ አሳሰበች

በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበትና በንፁኃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዲቆም አሜሪካ አሳሰበች

በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተመድ ጉባዔ ጎን ለጎን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የአፍሪካ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሞሊ ፊ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበት የመንግሥት ምላሽና ንፁኃን ላይ ያነጣጠረ የታጣቂዎች ጥቃት እንዲቆም አሳስበዋል። ረዳት ሚኒስትሯ ከሁለት ዓመታት በፊት የተካሄደውን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጸም፣ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር በመሆን ያለ ማቋረጥ ውትወታ እናደርጋለንም ብለዋል። በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያለውን ግጭት በተመለከተ ያለንን ሥጋት በመግለጽ እንዲቆም በግል በሚደረግ ውይይትና በይፋ በሚኖሩ መግለጫዎች እየጠየቁ መሆኑን አስታውቀዋል። ታጣቂዎች በንፁኃንና በመንግሥት መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እያደረሱ መሆኑን የገለጹት ሞሊ ፊ የመንግሥት…
Read More
በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ

በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ

አንድ ዓመት ሊሞላው ጥቂት ቀናት የቀሩት የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት አሁንም የቀጠለ ሲሆን እስራኤል እና የሊባኖሱ ሂዝቦላህ አዲስ ጦርነት ጀምረዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ከሚኖሩባቸው የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሊባኖስ ዋና ከተማዋ ቤሩትን ጨምሮ ሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች በእስራኤል የአየር ላይ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡ ይህን ተከትሎም በሊባኖስ የሚኖሩ ከ30 ሸህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከቀሪው የሀገሪቱ ዜጎች ጋር የደህንት ስጋት ውስጥ ወድቀዋል፡፡ በሊባኖስ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ህይወታቸውን እንዴት እየመሩ ይሆን ሲል የሀገሪቱ መዲና በሆነችው ቤሩትን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ጠይቋል፡፡ ለደህንነቷ በመስጋት ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች አንድ ኢትዮጵያዊ እንዳለችን ከሆነ ነበለት በሚባለው ቦታ ትኖር እንደነበር ነግራናለች፡፡ በአካባቢው ተከታታይ የእስራኤል የአየር ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ተከትሎ ወደ…
Read More
በአማራ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ከ160 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ከ160 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ጋምቤላ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ላይ ከህግ ውጪ ግድያ፣ የዘፈቀደ እስር፣ እገታ፣ አስገድዶ መድፈር እና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በንጹሀን ላይ ተፈጽመዋል ብሏል፡፡ ከሰኔ ወር ጀምሮ ባሉት ሶስት ወራት ውስጥ በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረው ጦርነት ከ160 በላይ ዜጎች መገደላቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል፡፡ ግድያ ከተፈጸመባቸው ዜጎች መካከል የአዕምሮ ህመምተኞች፣ አዛውንቶች፣ ህጻናት እና ሴቶች እንደሚገኙበት ተገልጿል፡፡ ጎንደር፣ የጎጃም አካባቢዎች፣ ደብረሲና፣ አታዬ፣ ሸዋሮቢት እና ሌሎችም ቦታዎች ያሉ ሲሆን መረጃ ለፋኖ ትሰጣላችሁ፣ የመንግስት ጉዳይ አስፈጻሚ…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ማስተላለፍ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ማስተላለፍ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ

ኩባንያው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ለዘመድ አዝማድ የሚልኩትን ገንዘብ (ሪሚታንስ) በማስተላለፍ አገልግሎት ላይ ለመሠማራት ማቀዱን አስታውቋል። ኩባንያው በዘርፉ መሠማራት የፈለገው፣ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ለውጡ በመደበኛውና በትይዩ ገበያው መካከል ያለውን የምንዛሬ ልዩነት ማጥበቡን ተከትሎ ነው ኩባንያው፣ ኬንያና ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሪሚታንስ አስተላላፊነት ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን ከዓለማቀፉ ገንዘብ አስተላላፊ ኩባንያ ዳሃብሺል ጋር ባለፈው ሐምሌ የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል። የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት የሆነው ኤምፔሳ (M-PESA) ከአንድ ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የአገልግሎት ፍቃድ ካገኘ ከሦስት ወራት በኋላ ስራ መጀመሩ አይዘነጋም። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለኔትወርክ ማስፋፊያ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መድቤያለሁ ብሏል፡፡ ተቋሙ አክሎም በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎችበተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ…
Read More
ኢትዮጵያ የቁም እንስሳትን ለወጪ ገበያ በባቡር ማጓጓዝ ጀመረች

ኢትዮጵያ የቁም እንስሳትን ለወጪ ገበያ በባቡር ማጓጓዝ ጀመረች

ኢትዮጵያ የቁም እንስሳት ወጪ ንግድ ወደ ጅቡቲ በባቡር ለመጀመሪያ ጊዜ ማጓጓዝ ጀመረች ከዚህ በፊት ወደ ሀገር ዉስጥ ገቢ ምርቶችን ለማስገባት ብቻ ያገለገል የነበረዉ የአዳማ - ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት አሁን ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የቁም እንስሳትን ማጓጓዝ ጀምሯል። የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ እንደገለፁት በአዳማ በኩል የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርትን ወደ ውጭ ሀገራት ጥራት ያለውን የስጋ ምርት የመላክ አቅምን ከመጨመሩም ባሻገር የትራንስፖርት መጨናነቅን ይቀንሳል። ከአዳማ ወደ ጅቡቲ የቁም እንስሳት የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ይፋ መሆኑን ያስታወቁት ስራ አስፈፃሚው ይህን አገልግሎት በመጀመራችን አቅማችን ከፍ ያደርገዋል ብለዋል። በባቡር ትራንስፖርት በመጠቀም ወደ ውጭ ሀገራት የሚላከው የእንስሳት ንግድ የህገወጥ ንግድ እንቅስቀሴንን ከማስቀረቱ ባለፈ ጊዜ…
Read More
የድቪ 2026 ማመልከቻ ከአንድ ሳምንት በኋላ ይጀመራል

የድቪ 2026 ማመልከቻ ከአንድ ሳምንት በኋላ ይጀመራል

የዓለማችን ልዕለ ሀያል የሆነችው አሜሪካ ከፈረንጆቹ 1995 ዓመት ጀምሮ በድቪ ሎተሪ አማካኝነት ወደ ሀገሯ በመውሰድ ለይ ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ለዚህ እድል ከተፈቀደላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን በየዓመቱ በአማካኝ ከ4 ሺህ እስከ 5 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ወደ አሜሪካ ያቀናሉ፡፡ የድቪ 2024 እድለኛ ኢትዮጵያዊን የቪዛ ማመልከቻቸው ከጥቂት ቀናት በኋላ የሚያበቃ ሲሆን የድቪ 2025 እድለኞች ደግሞ ከያዝነው መስከረም ወር መጠናቀቅ በኋላ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የቪዛ ጥያቄያቸውን ማቅረብ ይጀምራሉ፡፡ ይህ በዚህ እንዳለም የድቪ 2026 የማመልከቻ ጊዜ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚጀመር ሲሆን ለአንድ ወር እንደሚቆይ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት አስታውቋል፡፡ የማመልከቻ ጊዜው ከመስከረም 21 ቀን እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት 30 ቀናት ይቆያል የተባለ ሲሆን…
Read More
የኤርትራ ሰራዊት ተጨማሪ ቦታዎችን እየያዘ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባበለ

የኤርትራ ሰራዊት ተጨማሪ ቦታዎችን እየያዘ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባበለ

የኤርትራ ሰራዊት ቀደም ሲል ከያዛቸው አካባቢዎች ውጭ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባብሏል፡፡ የኤርትራ ሰራዊት ከጦርነቱ ወዲህ የያዛቸውን አካባቢዎች በማስፋፋት ከአዲግራት ከተማ በቅርብ ርቀት በ40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል መባሉን ያስተባበሉት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እኔ እስከማውቀው ድረስ የኤርትራ ሰራዊት ከነበረበት አልወጣም አዲስ የያዘውም መሬት ይለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሰራዊቱ ቀደም ሲልም ከነበረበት የዛላምበሳ አካባቢ እንዳልወጣ የገለጹት አቶ ጌታቸው እስካሁን ባለኝ መረጃ ወደ አዲግራትም ሆነ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ያደረገው አዲስ እንቅስቃሴ የለም ሲሉ ጥያቄውን አጣጥለዋል፡፡ በኤርትራ ሰራዊት የተያዘው አካባቢ የኢትዮጵያ መሬት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ጉዳዩን የመከታተል ኃላፊነት መሆን የነበረበት የፌዴራሉ መንግስት እንደሆነ በማስታወስም፤ ሆኖም መንግስት በአካባቢው…
Read More
ኢትዮጵያ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች

ኢትዮጵያ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ላይ ጥላው የነበረውን እገዳ አነሳች

ኢትዮጵያ ከአንድ ዓመት በፊት ለመዋዕለ ህጻናት ወይም ኬጂ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋ እንዳይማሩ ከልክላ ነበር፡፡ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የኬጂ ተማሪዎች እንዳይማሩ አግዶት የነበረውን እንግሊዘኛ ቋንቋ በድጋሚ እንዲሰጥ መወሰኑ ተገልጿል፡፡ ቢሮው በእንግሊዘኛ ቋንቋ ላይ ክልከላ የጣለው ህጻናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ በሚል እንደነበር በወቅቱ ገልጾ ነበር፡፡ ባለፈው ዓመት ተቋርጦ የነበረው የቅድመ መደበኛ (ኬጂ) የእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት፤ በዚህ ሳምንት በተጀመረው የ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን በሳምንት ለአምስት ጊዜ እንደሚሰጥ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ለቅድመ መደበኛ ትምህርት ያዘጋጀው የእንግሊዘኛ ቋንቋ የተማሪዎች መፅሐፍ እና የመምህራን መምሪያ ለመንግሥት ትምህርት ቤቶች ተሰራጭቷል። ሕጻናት ወደ አንደኛ ክፍል ከመሸጋገራቸው አስቀድሞ ባለው ቅድመ መደበኛ ደረጃ ለሚማሩ…
Read More
በአማራ ክልል ከአምስት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አልተመለሱም ተባለ

በአማራ ክልል ከአምስት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አልተመለሱም ተባለ

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ እንዳስታወቀው በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ አቅዶ ነበር፡፡ ይሁንና ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ተማሪዎች 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ " ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 292 ሺሕ በላይ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 1.2 ሚሊዮን በላይ፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ 180 ሺሕ ተማሪዎች ተመዝግበዋል " ብሏል፡፡ " በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምዝገባው እየተካሄደ ነው፡፡ ትንሽ እሱ ላይ መዘግየት ይታያል፡፡ እስካሁን በጠቅላላ ወደ 1.7 ሚሊዮን ተማሪዎች ናቸው የተመዘገቡት የእቅዱን ወደ 24 ፐርሰንት…
Read More
የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ለማድረግ ወሰነ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ለማድረግ ወሰነ

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ እንዲካሄድ መወሰኑ ይፋ ተደርጓል። ጉባዔው ዲሞክራቲክ ኮንጎ ላይ ለማድረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በቅርቡ በተከሰተው የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወረርሽኝ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መቀየሩን የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ጉባኤው አዲስ አበባ ላይ እንዲካሄድ ጥያቄ አቅርቦ በካፍ ተቀባይነት ማግኘቱን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል። በዚህም መሰረት የካፍ ጠቅላላ ጉባዔ በቀጣይ ጥቅምት ወር በመዲናችን አዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ይሆናል። ካፍ ዛሬ በሰጠው የቅድመ ጠቅላላ ጉባኤ ጋዜጣዊ መግለጫ የ2024 ቻን አፍሪካ ዋንጫ በሚቀጥለው የካቲት ወር በናይሮቢ ፣ ካምፓላ እና ዳሬ ሰላም እንደሚካሄድ አሳውቋል። የ2024 ቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በጥቅምት እና…
Read More