መነሻ ገፅ

በአረብ ሀገራት የሚገኙት አቦሸማኔዎች ከኢትዮጵያ የተሰረቁ ናቸው ተባለ

በአረብ ሀገራት የሚገኙት አቦሸማኔዎች ከኢትዮጵያ የተሰረቁ ናቸው ተባለ

በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ሀብት ላይ ከተደቀኑ በርካታ ችግሮች መካከል ህገወጥ የእንስሳት ዝውውር አንዱ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል። በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ  እንደተናገሩት ለተለያዩ አላማዎች ሲባል በኢትዮጵያ የሚገኙ የዱር እንስሳት ከነህይወታቸው በህገወጥ መንገድ ይዘዋወራሉ። በዚህ መልኩ ከሀገር የሚወጡ እንስሳቶች በርካታ ቢሆኑም  በቀዳሚነት አቦሸማኔ ይጠቀሳል ። አቦሸማኔ በተለይም በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል በሱማሌ ክልል መኖሪያውን በማድረጉ የአካባቢው ማህበረሰቦች ባካበቱት ተፈጥሮአዊ ዘዴ የአቦ ሸማኔ ቡችላዎችን በመያዝ ሶማሌላንድ አካባቢ ለሽያጭ እንደሚያቀርቡ ተጠቁሟል። በዚህ መልኩ ይህ እንስሳ ወደ መካከለኛው የአረብ ሀገራት ጭምር ላሉ ባለሀብቶች የሚሸጥበት ሁኔታ መኖሩን የገለፁት አቶ ዳንኤል ግለሰቦቹ የራሳቸው የሆነ መካነ አራዊት…
Read More
ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ሀገራቸው አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን ተናግረዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስተያየት ውድቅ አድርጓል። የጽህፈት ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሔ ፕሬዝዳንቱ ቱርዝ ሶሻል ተብሎ በሚጠራው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ዩናይትድ ስቴትስ የህዳሴ ግድብን በገንዘብ ደግፋለች ማለታቸውን "መሠረተ ቢስ" ብለውታል። ኃላፊው "ህዳሴ ግድብ ከ20ዐ3 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት፣ ጉልበት፣ እውቀትና በኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ ያለ ነው” ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል። አክለውም የአሜሪካው መሪ ንግግር ከዓለም አቀፋ ፖለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተናግረዋል። ከ15 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ…
Read More
በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሰሩ ተፈቀደ

በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሰሩ ተፈቀደ

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል። መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል። ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል። ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል። ብሔራዊ…
Read More
የመንግስት ተቋማት ስራ ለለቀቁና ለሞቱ ሰራተኞች ከ400 ሺህ በላይ ብር ደመወዝ ከፍለዋል ተባለ

የመንግስት ተቋማት ስራ ለለቀቁና ለሞቱ ሰራተኞች ከ400 ሺህ በላይ ብር ደመወዝ ከፍለዋል ተባለ

የፌደራል ዋና ኦዲተር የመንግስት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ዋና ኦዲተር በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 17 የመንግስት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሰራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ ከፍለው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ  በስተቀር የሰራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መስሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ በቋሚ የሥራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋልም ተብሏል፡፡ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ፣ ሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣…
Read More
ኢትዮጵያ ከሁለት ወር በኋላ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሁለት ወር በኋላ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተገለጸ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከቀጣዩ መስከረም ወር ጀምሮ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ መናገራቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ዘግቧል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ካሉ የሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ከመስከረም ወር ጀምሮ ነዳጇን ለገበያ ማቅረብ እንደምትጀምር ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰባት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪክ ነዳጅ ማውጣት ጀመረች በሚል ለኢትዮጵያዊያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡ ይሁንና ይህ ከሆነ ከሰባት ዓመት በኋላ ኢትዮጵያ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሶማሊ ክልል ኦጋዴን አካባቢ ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ እንዳላት በተደጋጋሚ ሲገለጽ የቆየ ሲሆን የቻይና ፖሊሲጂኤል ኩባንያ ነዳጅ ለማውጣት በሂደት ላይ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ የነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ…
Read More
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ትስስር ኩባንያዎች ቢሯቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ጠየቀች

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ትስስር ኩባንያዎች ቢሯቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ጠየቀች

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እንደ ሜታ (ፌሰቡክ) ያሉ የማኅበራዊ ትስስር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቅርጫንፍ ቢሮዎቻቸውን በኢትዮጵያ እንዲከፍቱ ጠይቋል፡፡ ባለሥልጣኑ በበይነ መረብ የሚካሄዱ የጥላቻ ንግግችን የሚመለከት የአንድ ዓመት ሪፖርቱን የተመለከተ መግለጫ ለመገናኛ ብዙኃን ሰጥቷል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን "እንደ ፌስቡክ ያሉ ድርጅቶች ከፍተኛ ተጠቃሚ ባለው ኢትዮጵያ ለማስታወቂያ ገቢ እያስገኙ አይደለም" ብሏል። ኢትዮጵያ ከ44 ሚሊዮን በላይ የበይነ ተጠቃሚዎች ያሉባት ሀገር ብትሆንም፤ እስካሁን ድረስ የማኅበራዊ ሚዲያ ፖለሲም ሆነ አዋጅ የላትም። ባለሥልጣኑ ለሦስተኛ ግዜ እንዳዘጋጀው በተገለጸው ሪፖርት ላይ፤ የጥላቻ ንግግር ከምንጊዜውም በላይ በበይነ መረብ አማካኝነት መስፋፋቱን ያሳያል ብሏል። ከጥር 2016 ዓ.ም. እስከ ጥር 2017 ዓ.ም. ያለውን የአንድ ዓመት ሪፖርት መቅረቡን ለመገናኛ ብዙኃን የገለጹት መግለጫውን…
Read More
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፕሬዝዳንት ትራምፕ አቀባበል ተደረገላቸው

አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፕሬዝዳንት ትራምፕ አቀባበል ተደረገላቸው

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተ-መንግሥት ተገናኝተው ተወያይተዋል ። በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተ-መንግሥት ተገናኝተው ተወያይተዋል። አምባሳደር ብናልፍ ነጩ ቤተ-መንግሥት ሲደርሱ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያንጸባርቅ ዲፕሎማሲያዊ አቀባበል እንደተደረገላቸው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ይህ የመጀመሪያ ግንኙነት በቀጣይ ጊዜያት ለሚደረጉ ውይይቶች መጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል የተባለም ሲሆን፤ አምባሳደሩ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር ተገናኝተው ስላደረጉት ውይይት በይፋ የተገለጸ ነገር የለም ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፤ በሁለቱ አገራት መካከል እንደ ሰላም፣ ጸጥታና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ጠንካራ አጋርነት ከመፍጠር አንጻር ያሉ ዕድሎችም ሰፊ…
Read More
ሩሲያ ለኢትዮጵያ ባህር ሀይል ድጋፍ እያደረገች መሆኑ ተገለጸ

ሩሲያ ለኢትዮጵያ ባህር ሀይል ድጋፍ እያደረገች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሩሲያ ድጋፍ እያከናወነችው የሚገኘው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነው ተብሏል። ኢትዮጵያ በሩሲያ ድጋፍ በአዲስ አበባ ከተማ ጃንሜዳ አካባቢ እያከናወነችው የሚገኘው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ 95 በመቶ መጠናቀቁ ተነግሯል። በሦስት ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ባለ አራት ፎቅ ሕንጻ ሲሆን፤ የአስተዳደር ቢሮዎች፣ የሕክምና ክሊኒክ፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ያካተተ ስለመሆኑ ስፑትኒክ አፍሪካ ዘግቧል። ይህም ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ቀጣናዊ ተጽዕኖ መልሳ ለማግኘት የምትከተለው ሰፊ ስትራቴጂ አካል ነው የተባለ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በታቀደለት ጊዜ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅም ተነግሯል። በተያዘው ዓመት መጋቢት ወር ላይ ኢትዮጵያ የባህር…
Read More
ኢትዮጵያ ለእዳ ክፍያ 463 ቢሊዮን ብር መመደቧ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ለእዳ ክፍያ 463 ቢሊዮን ብር መመደቧ ተገለጸ

የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ፣ ለ2018 በጀት ዓመት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ወይም 14 ቢሊዮን ዶላር ረቂቅ የፌደራል በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል። ረቂቅ በጀቱ እየተጠናቀቀ ካለው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ31 በመቶ ብልጫ ያለው ነው። ከቀረበው ረቂቅ በጀቱ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮኑ ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮኑ ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮኑ ለክልሎች ድጎማና 14 ቢሊዮኑ ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል መመደቡን ሚንስትሩ አብራርተዋል። ከጥቅል አገራዊ ምርት አንጻር 2 ነጥብ 2 በመቶ ያልተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥማል ተብሎ እንደሚጠበቅና ኾኖም መንግሥት ጉድለቱን ለመሙላት ከብሄራዊ ባንክ ብድር እንደማይበደር ተገልጧል። ይህ በዚህ እንዳለ መንግስት ከያዘው በጀት አንድ ሶስተኛውን ለእዳ ክፍያ መያዙ…
Read More
አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መፅሀፍ ተፃፈለት

አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መፅሀፍ ተፃፈለት

የአትሌት ኃይሌን የህይወትና የስራ ፍልስፍና የሚያስረዳውን መፅሀፍ የፃፈችው ልጁ ሜላት ኃይሌ ገብረስላሴ ናት። ረዳት ፀሀፊው ደግሞ አባዮሚ ሮቲሚ  የተባለ ፀሀፊ መሆኑን ሰምተናል። በ12 ምዕራፍ ተከፋፍሎ የተዘጋጀውን መጽሀፍ ለማሳናዳት ሁለት ዓመት እንደፈጀ ፀሀፊዋ አስረድታለች። አትሌት ኃይሌ ብዙውን የህይወት ታሪኩን ህዝብ የሚያውቀው ቢሆንም መፃህፉ የሚያተኩረው የህይወትና የስራ ፍልስፍናው ላይ እንደሆነ ተነግሯል። ለዚህም ልጁ እንደመሆኗ ከሌሎች ሰዎች በተለየ የአትሌት ሀይሌ ህይወት ለማወቅና ለመፃፍ እንዳስቻላት ሜላት ኃይሌ ጠቅሳለች። መፅሀፉ አትሌት ከእድገቱ እስከ አሁን ባለው የሯጭነትና የቢዝነስ ምዕራፍ የተከተላቸውን አመለካከቶቹን፣ ፍልስፍናውን፣ የህይወት ልምዱ የተካተተበት መሆኑን ልጁ ሜላት ተናግራለች። ለጊዜው ''Dissecting Haile' በሚል ርዕስ ለህትመት የሚበቃው መፅሀፋ ወደፊት ወደ ወደ አማርኛ እና ሌሎች ቋንቋዎች እንደሚተረጎም ተነግሯል።…
Read More