google

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ትስስር ኩባንያዎች ቢሯቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ጠየቀች

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ትስስር ኩባንያዎች ቢሯቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ ጠየቀች

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን እንደ ሜታ (ፌሰቡክ) ያሉ የማኅበራዊ ትስስር አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቅርጫንፍ ቢሮዎቻቸውን በኢትዮጵያ እንዲከፍቱ ጠይቋል፡፡ ባለሥልጣኑ በበይነ መረብ የሚካሄዱ የጥላቻ ንግግችን የሚመለከት የአንድ ዓመት ሪፖርቱን የተመለከተ መግለጫ ለመገናኛ ብዙኃን ሰጥቷል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን "እንደ ፌስቡክ ያሉ ድርጅቶች ከፍተኛ ተጠቃሚ ባለው ኢትዮጵያ ለማስታወቂያ ገቢ እያስገኙ አይደለም" ብሏል። ኢትዮጵያ ከ44 ሚሊዮን በላይ የበይነ ተጠቃሚዎች ያሉባት ሀገር ብትሆንም፤ እስካሁን ድረስ የማኅበራዊ ሚዲያ ፖለሲም ሆነ አዋጅ የላትም። ባለሥልጣኑ ለሦስተኛ ግዜ እንዳዘጋጀው በተገለጸው ሪፖርት ላይ፤ የጥላቻ ንግግር ከምንጊዜውም በላይ በበይነ መረብ አማካኝነት መስፋፋቱን ያሳያል ብሏል። ከጥር 2016 ዓ.ም. እስከ ጥር 2017 ዓ.ም. ያለውን የአንድ ዓመት ሪፖርት መቅረቡን ለመገናኛ ብዙኃን የገለጹት መግለጫውን…
Read More
ጎግል ፕሌይ ኢትዮጵያዊን ባለሙያዎችን መቀበል ጀመረ

ጎግል ፕሌይ ኢትዮጵያዊን ባለሙያዎችን መቀበል ጀመረ

የጎግል ፕሌይ አልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል ጀምሯል። ኢትዮጵያውያን አልሚዎች በጎግል ፕሌይ ላይ ተቀባይነት ማግኘተቻው የተለያዩ መተግበሪያዎችን እያለሙ ዓለም አቀፍ ደንበኞችን እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከጎግል ኩባንያ ጋር ያደረጋቸው ተደጋጋሚ ጥረቶች ለዚህ እንዳበቃቸው ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያዊያን የአይሲቲ ባለሙያዎች የGoogle Playን አለምአቀፍ ታዳሚዎች በቀጥታ በማስገኘት መተግበሪያዎቻቸው ሰፊ እይታን እንዲያገኝ እና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስችላልም ተብሏል፡፡ ይህ ምዕራፍ የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ተሰጥኦ ባለቤቶች መተግበሪያዎቻቸውን በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ ዲጂታል መድረኮች ላይ እንዲያትሙ አዲስ እድሎችን የሚከፍት እንደሆነም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ ዶ/ር እንዳሉት መንግስት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለመገንባት በርካታ ተነሳሽነቶችን በመተግበር እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህ አዲስ ጅማሮ…
Read More