Blog

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

የመደ ወላቡ ዩንቨርሲቲ 20 መምህራን በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ መምህራኑን ይዞ ሲጓዝ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 20 ደርሷል። ዛሬ ረፋድ የመደ ወላቡ መምህራንን ይዞ ሲጓዝ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር 20 መድረሱን ዩንቨርሲቲው አስታውቋል። የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ዛሬ ማለዳ ለማስተማር ወደ ሻሸመኔ ካምፓስ በመጓዝ ላይ እያሉ የትራፊክ አደጋ ደርሶባቸዋል። መምህራኑን የጫነው ተሸከርካሪው መንገድ ስቶ ወደ ገደል በመግባቱ በተፈጠረው በዚህ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ ይገኛል። ከአደጋው በሕይወት የተረፉት ሌሎች ሰዎች በአደባ፣ ዶዶላ እና ሮቤ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ኢብራሂም…
Read More
ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ከቀረጥ ነጻ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በፊት ያሻሻለችውን የኤክሳይስ ታክስ ህግን ዳግም ማሻሻያ አድርጋለች። በተቻቻለው ህግ ሙሰረት ከዚህ በፊት ከፍተኛ ግብር የተጣለባቸው ምርቶች ከፍተኛ የሚባል የግብር ቅናሽ ተደርጎባቸዋል። እንዲሁም ከዚህ በፊት ግብር ያልተጣለባቸው ምርቶች ላይ ጭማሪ ከተደረገባቸቅ ምርቶች መካከል የሞባይል አገልግሎቶች (ኢንተርኔት ፣ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክት)፣  የገመድ አልባ ስልክ አገልግሎት፣ የገመድም ሆነ ገመድ አልባ የኢንተርኔት አገልግሎቶች የ 5 በመቶ ግብር ተጥሎባቸዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ግን የኤክሳይዝ ታክስ ማስከፈያ ዋጋቸው የቀነሰ ምርቶች ስኳር ለህክምና ከሚውለው በስተቀር የ10 በመቶ ቅናሽ እንደተደረገባቸው ተገልጿል፡፡ ማስቲካ ፣ቸኮሌት እና ጣፋጭ ከረሜላ ምርቶች ከዚህ በፊት 20 በመቶ የኤክሳይስ ታክስ ተጥሎባቸው የነበሩ ሲሆን አሁን የ10 በመቶ ቅናሽ ከተደረገባቸው  ምርቶች መካከል ናቸው፡፡…
Read More
በሸገር ከተማ አስተዳድር ከ10 በላይ መስጅዶች መፍረሳቸው ተገለጸ

በሸገር ከተማ አስተዳድር ከ10 በላይ መስጅዶች መፍረሳቸው ተገለጸ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በጉዳዩ ዙሪያ ጣልቃ እንዲገቡ  ተጠይቀዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በቅርቡ በአዲስ አበባ ዙሪያ "ሸገር ከተማ" ተብሎ በተመሠረተው ከተማ መስጅዶች እየፈረሱ መሆናቸውን ገልጿል። የመስጂድ ፈረሳው መቀጠሉን ተከትሎም  "አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጠው" የሚጠይቅ ደብዳቤ ምክር ቤዩ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጽፏል። ምክር ቤቱ በደብዳቤው፤ በከተማ አስተዳደሩ "ህገወጥ" በሚል በርካታ መስጂዶች እየፈረሱበት እንደሚገኙና፣ በጉዳዩ ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጋር በስልክ በመነጋገር መፍትሄ ላይ ደርሶ እንደነበር ገልጿል። ነገር ግን "የከተማ አስተዳደሩ በረመዳን ወር ለጊዜው የመስጂድ ፈረሳውን እንዲቆም በማድረግ ከረመዳን በኋላ የመስጅዶች ፈረሳ በአዲስ መልከ በብዛት ቀጥሏል"  ብሏል። ምክር ቤቱ በመግለጫው የመስጅድ ፈረሳ ጉዳይ በከተማ አስተዳደሩ "ህገ ወጥ" ስለተባለ…
Read More
ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲዋን ከማለዘብ ወደ ማሳመን መቀየሩን ገለጸች

ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲዋን ከማለዘብ ወደ ማሳመን መቀየሩን ገለጸች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ኢትዮጵያ በሰሜኑ ጦርነት ውስጥ በነበረችበት ወቅት  የደረሱ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ለመቋቋም "የማለዘብ ዲፕሎማሲ" ስትከተል መቆየቷን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ እና ተጨማሪ የዲፕሎማሲ ስራዎች በመሰራታቸው ይደርሱ የነበሩ ጫናዎች መቀነሳቸውን ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከማለዘብ ዲፕሎማሲ ወደ ማሳመን ዲፕሎማሲ መመለሷን የተናገሩት አምባሳደር መለስ የተለያዩ የዓለማችን ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻሻል መሪዎቻቸውን ወደ አዲስ አበባ በመላክ ላይ መሆናቸውን አክለዋል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ ከተማም ከኒዮርክ እና ጀኔቫ በመቀጠል ሶስተኛዋ የዓለማችን የዲፕሎማሲ ከተማ ይዞታዋ መመለሷን ቃል…
Read More
በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

በጉና ተራራ ላይ የህዋ ማዕከል የመገንባት እቅድ እንዳለ ተገለጸ

የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በአፄ ቴውድሮስ የተሰየመች ሮኬት ለኹለተኛ ጊዜ ማስወንጨፉ ይታወሳል። ዩንቨርሲቲው በከተማዋ አቅራቢ በሚገኘው የጉና ተራራ ላይ የህዋ ምርምር ማዕከል ለመገንባት እቅድ መያዙን ገልጿል። 154ኛውን የአፄ ቴዎድሮስ ዝክረ-ሰማዕት መታሰቢያ በዓል አስመልክቶ የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ትምህርት ዘርፍ በአካባቢያቸው ባለ ቁሳቁስ ከ 2 ኪ.ሜትር በላይ መወንጨፍ የቻለች ሮኬት ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንድ ዓመት በፊት አስወንጭፏል። ዩንቨርሲቲው በዚህ ዓመትም በተሻለ መልኩ ማስወንጨፍ መቻላቸውን ዩንቨርሲቲው ገልጿል። የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር አዲሱ ወርቁ እንዳሉት በ2014 የተሰሩት ሮኬትና መድፍ  ዋና አላማ የአጼ ቴዎድሮስን የመቅደላ መድፍን ለመድገምና ኢትዮጽያ ውስጥ የተሳካለት ሮኬትና መድፍ መስራት መቻል እንደሆነ ተናግረዋል።  ሚያዚያ 2014 በሮኬት ሳይንስ ማዕከል አሞራ ገደል ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተወነጨፈችው ሮኬት የት…
Read More
በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ ወደ አራት ክልሎች ተዛመተ

በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ ወደ አራት ክልሎች ተዛመተ

በሳሙኤል አባተ የኮሌራ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች መዛመቱን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። በደቡብ ክልል ልዩ ልዩ ዞኖች እና ወረዳዎች ደግሞ በወረርሽኙ ከተጠቁ 920 ሰዎች መካከል የ18 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል። የጤና ጥበቃ ሚንስቴርም ወረርሽኙ በተስፋፋባቸው አካባቢዎች ክትባት መስጠት ተጀምሯል። በኢትዮጵያ፣ የኮሌራ ወረርሽኝ፣ በአራት ክልሎች መዛመቱን ያስታወቀው የጤና ሚኒስቴር፣ ወረርሽኙን ለመከላከል፣ ለ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ክትባት እንደሚሰጥ አመልክቷል፡፡ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ተዛምቶ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘው ይህ ወረርሽኝ በዐዲስ መልክ በተከሠተባቸው የደቡብ ክልል አምስት ዞኖች እና ሦስት ልዩ ወረዳዎች ተስፋፍቷል ተብሏል። የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ወረርሽኙ፥ በአገር አቀፍ ደረጃ በአራት ክልሎች መከሠቱን አረጋግጠዋል። ወረርሽኙ ከተስፋፋባቸው ክልሎች መካከልም ኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሶማሊ…
Read More
ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተርሚላን ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተርሚላን ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

በአውሮፓ ምርጥ እግር ኳስ ክለቦች ሙካከል ሲካሄድ የቆየው የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ተፋላሚዎች ታውቀዋል። ትናንት ምሽት በእንግሊዝ ማንችስተር ከተማ በሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ መካከል የተካሄደው ውድድር በሲቲ የበላይነት ተጠናቋል። በርናርዶ ሲልቫ ሁለት ጎል፣ አልቫሬዝ እና ሚሊታኦ በራሱ ግብ ላይ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ሲቲ በቱርክ ኢስታምቡል ከተማ ለሚካሄደው የፍጻሜ ውድድር ማለፍ ችሏል። የጣልያኑ ኢንተር ሚላን በፍጻሜው ማንችስተር ሲቲን የሚገጥም ሲሆን ጨዋታው ሰኔ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት 4:00 ላይ ይካሄዳል ተብሏል። የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ውድድርን የስፔኑ ሪያል ማድሪድ 14 ጊዜ በማሸነፍ ቀድሚው ክለብ ሆኖ ተመዝግቧል። የፍጻሜ ተፋላሚው ማንችስተር ሲቲ እስካሁን አንድም ጊዜ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግን ያላሸነፈ ሲሆን ሌላኛው የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተርሚላን ሶስት…
Read More
በኢትዮጵያ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች የረሀብ አድማ ጀመሩ

በኢትዮጵያ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች የረሀብ አድማ ጀመሩ

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች እና ምሁራን የረሃብ አድማ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። መንግሥትን በኃይል ለመጣል አሲረዋል በሚል የሽብርተኝነት ክስ ቀርቦባቸው በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች እና ምሁራን የረሃብ አድማ ላይ መሆናቸውን የእስረኞቹ ቤተሰቦች ገለጹ። ተጠርጣሪዎቹ የረሃብ አድማውን የጀመሩት ከትላንት ጀምሮ ሲሆን፤ አድማው ለሦስት ተከታታይ ቀን የሚቆይ እንንደሆነ ተገልጿል። የረሃብ አድማው ላይ ከሚገኙት እስረኞች መካከል ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሳሳይ፣ መምህርት መስከረም አበራ፣ ረዳት ፕ/ር ሲሳይ አውግቸው፣ ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ እና ሌሎች የሽብር ክስ የቀረበባቸው ታሳሪዎች ይገኙበታል። የአድማው ምክንያት ከእነሱ እስር በተጨማሪ በምንም ጉዳይ ላይ ተሳትፎ የሌላቸው ሰዎች በብዛት የሚታሰሩበትን ሁኔታ ለመቃወም ነውም ተብሏል። የፌደራል መንግሥት ጸጥታ እና ደኅንነት የጋራ…
Read More
የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አሸነፉ

የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አሸነፉ

አቢሲኒያ ባንክ ለሶስት እንስቶች አንድ ሚሊዮን ብር ሸለመ ባንኩ "አሚን አዋርድ" በሚል የሰየመውን የሥራ ፈጠራ ውድድር አጠናቋል፡፡ ውድድሩ ካሳለፍነው ህዳር ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ በሥራ ፈጠራቸው ይዘት እና ችግር ፈቺነታቸው ለተመረጡ 5 ተወዳዳሪዎች የእውቅናና የሽልማት መርሐ-ግብር በአዳማ ከተማ ተካሂዷል፡፡ በውድድሩ ላይ ከ1ኛ - 5ኛ ለወጡ ተሳታፊዎች በአጠቃላይ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የተሸለሙ ሲሆን ከ6ተኛ እስከ 20ኛ ድረስ ለወጡ ተሳታፊዎችም የማበረታቻ ሽልማት መሰጠቱን አቢሲኒያ ባንክ ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ የአንደኝነት ደረጃን በማግኘት የ1,000,000 ብር ተሸላሚ የሆኑት በአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩ ሦስት እንስቶች አሸንፈዋል፡፡ እንስቶቹ ‹ግሪን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ማዳበሪያ› በሚል በጋራ ባቋቋሙት ድርጅት ስም አሸናፊ በመሆን ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል፡፡
Read More
ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ደርጅቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት ውስጥ 10 ሺህ ቤቶችን እንደሚገነባ አስታውቋል፡፡ ከ30 አመታት በላይ በመኖሪያ ቤት ግንባታ እና በኮንስትራክሽን ዘርፉ የተሰማራዉ ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለገበያ ማቅረቡን አስታዉቋል። የፍሊንትስቶን መስራችና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጸደቀ ይሁኔ እንደተናገሩት ከ20 ሺህ ብር ጀምሮ እስከ 2 ሚሊዮን ብር ድረስ ዋጋ ያላቸዉን አክሲዮኖች ለሽያጭ መቅረባቸዉን ተናግረዋል። የአንዱ አክሲዮን ዋጋም 1 ሺህ ብር መሆኑን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ከሚቀጥለው ሐምሌ ጀምሮ ሽያጩ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ባለ አክሲዮኖች ባላቸዉ የድርሻ መጠን ተሰልቶ አልያም በፍላጎታቸዉ ተጨማሪ ገንዘብ ከፍለዉ የቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት እድል መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡ በዋነኛነት አክሲዮን ሽያጩ ያስፈለገዉ ተጨማሪ ካፒታል ለማግኘት ፣ ድርጅቱን ከ አምስት ሰዎች የሽርክና ባለቤትነት…
Read More