Blog

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 100 ሚሊዮን መንገደኖችን የሚያስተናገድ ኤርፖርት ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 100 ሚሊዮን መንገደኖችን የሚያስተናገድ ኤርፖርት ሊያስገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ ለመገንባት በሂደት ላይ መሆኑን አስታውቋል። በዓመት 100 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው አውሮፕላን ጣቢያ በቢሾፍቱ ከተማ እንደሚገነባ ገልጿል። ይህ አውሮፕላን ጣቢያ ወይም ኤርፖርት የሚገነባው በዓመት 25 ሚሊዮን መንገደኞችን ብቻ የማስተናገድ ያለው ቦሌ ዓከም አቀፍ ኤርፖርትን ለመተካት እንደሆነ የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል። በቢሾፍቱ ልዩ ስሙ አቡ ሴራ በተባለው ስፍራ የሚገነባው ይህ ኤርፖርት ግንባታ ዲዛይን ዳር የተሰኘው ኩባንያ መመረጡንም አቶ መስፍን ገልጸዋል። አቶ መስፍን አክለውም አዲሱ ኤርፖርት ግንባታ በአምስት ዓመታት ውስጥ በሁለት ዙር ይገነባል ያሉ ሲሆን ለመጀመሪያው ዙር ግንባታ ስድስት ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታልም ብለዋል። ኤርፖርቱ ባንድ ጊዜ አራት አውሮፕላኖችን የማሳረፍ እና መንደርደሪያ…
Read More
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክተዋል። የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክታለች። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለአሜሪካዊያን አገልግሎት የሰጡ ተቋማትን እና ግለሰቦችን የህይወት ዘመን ሽልማት ይሰጣል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 25 ዓመታት በአሜሪካ ለሚኖሩ ዜጎች በሰጠው አገልግሎት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኗል። አየር መንገዱ ሽልማቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ "ሽልማቱ ለሰጠው አገልግሎት እውቅና የሰጠ ነው" ብሏል። ፕሬዝዳንት ባይደን የፈረሙበት ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮች በአትላንታ በተዘጋጀ መርሀግብር ላይ ተቀብለዋል ተብላል። የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱ ባለፉት ዓመታት ለሰጠው የአቪዬሽን አገልግሎት እውቅና ባለፈ ዓለም አቀፍ ትብብሮችን እንዲያሰፋ…
Read More
አዲስ አበባ ዓለም-አቀፍ የቦክስ ውድድር ልታስተናግድ ነው

አዲስ አበባ ዓለም-አቀፍ የቦክስ ውድድር ልታስተናግድ ነው

የአፍሪካ ቦክስ ኮንፌደሬሽን ዋና ቢሮውን በአዲስ አበባ የከፈተ ሲሆን፣ ቅዳሜ ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በደማቅ ዝግጅት በይፋ ያስመርቃል፡፡ ፌዴሬሽኑ የቢሮውን መክፈት አስመልክቶ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ አለም አቀፍ የቦክስ ውድድር እንደሚዘጋክ ተገልጿል፡፡ ይህ አለም አቀፍ የቦክስ ውድድርን የአለም አቀፉ የቦክስ ማህበር ከአፍሪካ የቦክስ ኮንፌደሬሽን እንዲሁም ከኢትዮጵያ የቦክስ ፌደሬሽን ጋር በመተበበር በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይዘጋጃል ተብሏል፡፡ 20 ዓለም አቀፍ ፕሮፌሽናል ቦክሰኞች ከሩሲያ፣ ሜክሲኮ፣ እንግሊዝ፣ ካዛኪስታን፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተገልጿል፡፡ ይህ ልዩ የቦክስ ውድድር ላይ የተሳተፉ ቦክሰኞች በአፍሪካ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቶላቸዋል የተባለ ሲሆን ውድድሩ በ10 ዘርች ይካሄዳል ተብሏል፡፡ ይህ አለም-አቀፍ የቦክስ ውድድርን ለመዘገብ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላርን በ107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላርን በ107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ  ባንክ ለባንኮች ዶላር ለመሸጥ ያወጣው ልዩ ጨረታ ውጤትን ይፋ አድርጓል። በዛሬው እለት በተካሄደው ልዩ ጨረታ 27 ባንኮች የሚፈልጉትን የዶላር መጠን እና የሚገዙበትን ዋጋ አስገብተው ተጫርተዋል። ባንኮቹ ለአንድ የአሜሪካ ዶላር ያቀረቡት አማካይ የመግዣ ዋጋ 107.9 ብር መሆኑን ባንኩ ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ጨረታው በነገው እለት ባንኮች በሚያወጡት እለታዊ የውጭ ምንዛሬ ተመን ላይ ለውጥ እንዲመጣ እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብሏል ብሔራዊ  ባንክ። የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ የዶላር ሽያጭ ጨረታው ውጤትን ሲገልጹ ባለፉት ቀናት በባንኮች እና በብላክ ገበያው መካከል ያለው ልዩነት እየጠበበ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የውጭ ምንዛሬ መረጋጋትን ያመጣል ያሉት አቶ ማሞ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሁሉንም የውጭ ምንዛሬ እንቅስቃሴ ወደ ባንክ ስርአት የማስገባት እቅድ…
Read More
ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚኖሩ ዜጎቿን አስጠነቀቀች

ኢትዮጵያ በሊባኖስ የሚኖሩ ዜጎቿን አስጠነቀቀች

በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በቤሩት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል። እስራኤል የሃመስ መሪ ኢስማኤል ሃኒየህ እና የሊባሱ ሄዝቦላህ የጦር መሪ ፉአድ ችኩር መግደሏን ተከትሎ ኢራን በእስራኤል ላይ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ዝታለች። የኢራንን ዛቻ ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል በሚል ከፍተኛ ስጋት በመንገሱ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚደረጉ በረራዎች የተሰረዙ ሲሆን ሀገራትም ዜጎቻቸውን በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው። በቤሩት የሚገኘው የኢትዮጵያ የቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፤ በሊባኖስ እና በቀጠናው ያለው ወቅታዊ የፀጥታ ስጋት እና ውጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ መምጣቱን አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ በሊባኖስ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ደህንነት ለማስጠበቅ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን በትኩረት እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል። በዚህም መሰረት ኢትዮጵያውያን ጥንቃቄ እንዲያደርጉና…
Read More
የፌደራል መንግስት ዓመታዊ በጀት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

የፌደራል መንግስት ዓመታዊ በጀት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር ደረሰ

መንግስት 550 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት አዘጋጅቷል ከሁለት ወር በፊት 970 ቢሊዮን ብር ዓመታዊ በጀት አጽድቆ የነበረው የፌደራል መንግስት ግማሽ ትሪሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዳሉት የፌደራል መንግሥት 551 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ  ተናግረዋል። መንገስት ካቀረበው 550 ቢሊዮን ብር ውስጥ 240 ቢሊዮን ብሩ "ለማኅበራዊ ድጋፍ " የሚውል ነው የተባለ ሲሆን ቀሪው ደግሞ ለማህበራዊ ድጋፍ፣ ለምግብ ዋስትና፣ ለሰራተኛ ደመወዝ ጭማሪ፣ ለመድሃኒት ድጎማ፣ ለለነዳጅ ድጎማ እና ሌሎች መሰረታዊ ሸቀጦች ድጎማ እንደሚውል ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ የፌደራል መንግስት የበጀት ማስተካከያ ያደረገው ከዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ በብድር እና እርዳታ ማግኘቱን ተከትሎ ነው፡፡…
Read More
ራይላ ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ለመሆን እጩ ሆነው ተመዘገቡ

ራይላ ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ለመሆን እጩ ሆነው ተመዘገቡ

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ምርጫ በየአራት ዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት የህብረቱ ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሃማት ስልጣን ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ ቀርቶታል፡፡ ይህን ተከትሎም ህብረቱ ማስታወቂያ ያወጣ ሲሆን የኬንያ ፕሬዝዳንት ለመሆን አራት ጊዜ ተወዳድረው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በይፋ ጥያቄ አቀርበዋል፡፡ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የራይላ ኦዲንጋ ጥያቄን በአዲስ አበባ በይፋ ለአፍሪካ ህብረት አቅርቧል፡፡ የአፍሪካ ህብረት እጩ ተወዳዳሪዎች እንዲመዘገቡ ያስቀመጠው ጊዜ የፊታችን ማክሰኞ የሚያበቃ ሲሆን ኬንያ ራይላ ኦዲንጋን ዋነኛ እጩ አድርጋ አስመዘግባለች፡፡ ከኬንያ በተጨማሪ ጅቡቲ፣ ሲሸልስ እና ሶማሊያም እጩ ያስመዘገቡ ሲሆን ራይላ ኦዲንጋ የተሻለ ድምጽ ሊያገኙ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ እጩዎች ከተመዘገቡ በኋላ ኢትዮጵያዊቷ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጅት ስነጊዮርጊስ አባል የሆኑት የአፍሪካ…
Read More
ኢትዮጵያ ዜጎቿ ወደ ታይላንድ እና ማይናማር እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች

ኢትዮጵያ ዜጎቿ ወደ ታይላንድ እና ማይናማር እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች

ኢትዮጵያ ከታይላንድ እና ማይናማር ጋር ምንም አይነት የስራ ስምምነት እንደሌላት ገልጻለች የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ላይ እንዳሉት በርካታ ኢትዮጵያዊያን ወደ እስያዎቹ ታይላንድ እና ማይናማር በህገወጥ ደላሎች እየተታለሉ እየተጓዙ መሆኑን ተናግረዋል ። ኢትዮጵያዊያኑ ለስራ በሚል ወደ ሁለቱ ሀገራት እየተጓዙ መሆኑን አውቀናል ያሉት አምባሳደር ነብዩ ይሁንና ኢትዮጵያ ከተባሉት ሀገራት ጋር የስራ ስምምነት እንዳልተፈራረመች ተናግረዋል። በህገወጥ ደላሎች ተታለው ወደ ስፍራው የሄዱ እና በጉዳት ላይ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ለመርዳትም በቶኪዮ እና ኒው ዴልሒ ባሉ ኢምባሲዎች በኩል ጥረቶች በመደረግ ላይ እንደሆነ አምባሳደር ነብዩ ገልጸዋል። አምባሳደር ነብዩ በመግለጫቸው ላይ ያነሱት ሌላኛው ጉዳይ የኢትዮጵያ እና…
Read More
ጸረ ሙስና ኮሚሽን የ113 አመራሮችን ሃብት እያጣራ መሆኑን አስታወቀ

ጸረ ሙስና ኮሚሽን የ113 አመራሮችን ሃብት እያጣራ መሆኑን አስታወቀ

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በ2016 በጀት አመት ሃብታቸውን ካስመዘገቡት አመራሮች መካከል በተጨማሪም የሃብት ማጣራት ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ኮሚሽኑ በአንድ መቶ አስራ ሦስት ውሳኔ ሰጪ አመራሮች ላይ የሃብት ማጣራት ስራ እየሰራ መሆኑን የኮሚሽኑ የሙስና መረጃ አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን በላይነህ ተናረዋል፡፡ ያስመዘገቡት ሃብት አጠራጣሪ ሁኖ በተገኙና በተደረጉ ጥቆማዎች መሰረት በውሳኔ ሰጪ አመራሮች ላይ የሃብት ማጣራት ሥራ እየተሰራ እንዳለ ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡ ኮሚሽኑ በሚሰራው የሃብት ማጣራት ሥራ ሃታቸው ለሙስና የተጋለጡትን ለፍትህ ሚኒስቴር እንደሚሳውቅም ጠቁመዋል፡፡ ሃብታቸው እየተጣራ ያሉትን ውሳኔ ሰጪ አመራሮች በአሁኑ ሰዓት ይፋ ማድርጉ ያልተመዘገቡ ሃብቶችን እንዲያሸሹ ስለሚያደርግ ከማጣራት ሥራው በኋላ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ ከህብረተሰቡ ጋር በይበልጥ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ16 ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ16 ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ሰጠ

የዓለም ባንክ የዳይሬክቶች ቦርድ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለኢትዮጵያ የ16 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ብድር እና እርዳታ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡ የዓለም ባንክ በድረ ገጹ ባወጣው መግለጫው የገንዘብ ድጋፍና ብድሩ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ ለመደገፍ የሚውል መሆኑን አስታውቋል። በዚህ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ካጸደቀው ገንዘብ ውስጥ 1 ቢሊዮን ዶላር ቀጥተኛ ድጋፍ መሆኑን የገለጸው ባንኩ፤ 500 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ የተራዘመ ብድር ነው ብሏል። የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ እያከናወነችው ያለችውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለመደገፍ በርካታ የድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት 1 ቢሊዮን ዶላር የቀጥታ እርዳታ ሲሆን 500 ሚሊዮን ዶላር የእዳ ክፍያ ማራዘሚያ እንዲሁም 320 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ትብብር በሚል…
Read More