TPLF

በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን በግዴታ ትጥቅ ለማስፈታት እንቅስቃሴ በመጀመሩ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፤ በክልሉ ልዩ ኃይል እና በፌዴራል የጸጥታ ተቋማት መካከል ከፍተኛ ውጥረት መፈጠሩን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አስታወቀ፡፡ የክልሉን ልዩ ኃይል ያለ በቂ ዝግጅት፣ ውይይት፣ የጋራ መግባባትና መተማመን ሳይደረስ በድንገት እና ያለበቂ የጸጥታ ዋስትና ለማፍረስ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየሄደበት ያለው መንገድ ኃላፊነት የጎደለው መሆኑን አብን አስታውቋል፡፡ ጉዳዩ በአማራ ክልል ብቻ ሳይወሰን በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አለመረጋጋት የሚፈጥር፣ ክልሉን እና  ኢትዮጵያን ወደ ሌላ የቀውስ አዙሪት የሚከት አደገኛ አካሄድ መሆኑን አብን ለፌዴራሉ መንግሥትና ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አሳስቧል፡፡ በመሆኑም፣ የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ውሳኔውን በአፋጣኝ እንዲቀለብስ እና ከአማራ…
Read More
በትግራይ ክልል ሁለት የቀድሞ ጦር መሪዎች በምክትል ፕሬዝዳንትነት ተሾሙ

በትግራይ ክልል ሁለት የቀድሞ ጦር መሪዎች በምክትል ፕሬዝዳንትነት ተሾሙ

አዲስ በተቋቋመው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ እና ጀነራል ፃድቃን ገብረተንሳይ የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሾመዋል። ይኸው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው አዲሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር 27 አባላት ያሉትን ካቢኔ ይፋ ባደረገበት ወቅት ተገልጿል። በአዲሱ ካቢኔ ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የሰላም እና ጸጥታ ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ሆነው ሲሾሙ፣ ሌተናል ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ደግሞ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደር እና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ሆነዋል። ሹመቱ በመቐለ ከተማ ይፋ ሲደረግ የክልሉን መንግስት ሲመራ የነበረው የቀድሞ ካቢኔ፤ የአስፈጻሚነት ስልጣኑን በጊዜያዊ አስተዳደሩ ለተቋቋመው አዲሱ ካቢኔ አስረክቧል። አዲሱ ካቢኔ የተዋቀረው ከህወሓት፣ ከትግራይ ኃይሎች፣ ከምሁራን እና ከብሔራዊ…
Read More
የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦር አመራር መኮንኖች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል። ኤርትራ ወታደራዊ ልኡክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዓቅም እና እየተከናወኑ ያሉ የምርምር እና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና፤ ኢንስቲትዩቱ እያከናወናቸው ባሉ የቴክኖሎጂ ሥራዎች ዙሪያ ለቡድኑ አባላት ገለጻ ማድረጋቸውን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡ የኤርትራ የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦሩ አመራሮች ቡድን አስተባባሪ ጀነራል አብርሃ ካሳ፤ በኢንስቲትዩቱ ያደረጉት ጉብኝት ለአገራቸው ብዙ ልምድ የቀሰሙበት መሆኑን መናገራቸው ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በቴክኖሎጂው ዘርፍም አብረው መስራት የሚያስችላቸው እድል ስለመኖሩም የተገነዘቡበት ጉብኝት መሆኑን መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከ20 ዓመት በፊት ወደ ደም አፋሳሽ…
Read More
የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ መልቀቅ እንደሚጀምር የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል። ለክልሉ የሚለቀቀው በጀት፤ ለሌሎች ክልሎች እንደሚደረገው ሁሉ በወራት ተከፋፍሎ የሚላክ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት ለትግራይ በጀት ለማስተላለፍ ከስምምነት ላይ መድረሱን በተመለከተ አቶ ጌታቸው ረዳ ከቀናት በፊት ተናግረው ነበር። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙት አቶ ጌታቸው፤ የፌደራል መንግስት በጀት መፍቀዱን፤ ሆኖም የገንዘብ መጠኑን በተመለከተ ግን “ገና እንነጋገራለን” ማለታቸው ይታወሳል። የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው በበኩላቸው፤ የትግራይ ክልል በጀት “የሚታወቅ” መሆኑን ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እስኪቋቋም የበጀት ድጎማ ሳይለቅቅ ቢቆይም፤ በክልሉ ውስጥ…
Read More
መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ።

መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ።

መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ። የፍትህ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በፌዴራል መንግስት እና በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መሃከል በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት ከግጭቱ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወንጀሎች ተጠያቂነት በተመለከተ ያለውን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ሊታዩ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብላል። በመሆኑም በወንጀል ተጠርጥረዉ ክስ ቀርቦባቸዉ የነበሩ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮችን ክስ ማቋረጡን ሚንስቴሩ አስታውቃል። ክሱ የተቋረጠላቸው ተከሳሾች ጉዳያቸዉ በቀጣይ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ እንደሚታይም ተገልጿል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ቀርቦ በክርክር ሂደት ላይ ይገኙ የነበሩ የወንጀል ክሶች በአዋጅ 943/2008 አንቀጽ 6 (3) (ሠ) መሰረት መነሳታቸውን ሚንስቴሩ ገልጻል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት…
Read More
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባት (ህወሀት) በትግራይ ክልል ያለውን የሀገር መከላከያ ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተጀመረው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት ከ800 ሺህ በላይ ዜጎችን እና ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ የንብረት ውድመት አድርሷል። በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል የተደረገው ይህ ጦርነት ባሳለፍነው ህዳር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። ይህን ስምምነት ተከትሎም ጦርነቱ የቆመ ሲሆን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት በመመስረት ላይ ይገኛል። እንዲሁም ህወሀት በግንቦት 2021 ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ ነበር። ይህ ህግ አውጪ ምክር ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ህወሀትን ከሽብር መዝገብ ላይ ሰርዟል። የኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እና የአማራ…
Read More
ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ሕወሀት በሽብርተኝነት ከተፈረጀ ከ22 ወራት በኋላ ውሳኔው ተሽሯል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል። ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል። ለሰሜኑ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረትም በፌደራል መንግስት እና በህወሓት በኩል ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። ስምምነቱ የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ እና የሰብዓዊ እርዳታ ለተጎጂዎች እንዲቀርብ አድርጓል። ህወሓትም ታጣቂዎቹን ወደ ካምፕ በመሰብሰብ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን…
Read More
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በሚመለከት በአሜሪካ የወጣውን መግለጫ ውድቅ አደረገችየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ሁሉም ተሳታፊዎች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን አስታውቋል። ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል ሲል የደረሰችበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።  በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።  የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ…
Read More
ኢትዮጵያ ከጦርነት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ

ኢትዮጵያ ከጦርነት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ

ኢትዮጵያ በጦርነት ከደረሰባት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ በኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በፊት ህወሀት በሀገር መከላከያ የሰሜን እዝ ላይ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ ነበር ጦርነት የተነሳው። በዚህ ጦርነት ምክንያት 800 000 ዜጎች ህይወታቸው እንዳለፈ ሲገለጽ የግለሰቦች እና የመንግስት መሰረተ ልማቶች ወድመዋል። ጦርነቱ አሁን ላይ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የሰላም ስምምነት ተፈርሞ ጦርነቱ ቆሟል። ይህ ለሁለት ዓመት የዘለቀው ጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን እና ሌሎች ሀብቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የፋይናንስ ሚንስቴር ገልጿል። ጦርነቱ ክፉኛ የጎዳቸው ትግራይ ፣አማራ እና አፋር ክልሎች በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ከደረሰባቸው ጉዳት እንዲያገግሙ 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋልም ተብሏል። ይህ የመልሶ ግንባታ በጀት ከፌደራል መንግሥት ፣ ዓለም…
Read More
ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ከሰሞኑ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በአዲስ አበባ የነበሩት ጌታቸው ረዳ በትግራይ አዲስ የሚቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ በሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መመረጣቸው ተነግሯል። የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ (ቪኦኤ) የትግርኛው አገልግሎት ክፍል እንደዘገበው፣ ጌታቸው የማዕከላዊ ኮሚቴውን አብላጫ ድምጽ አግኝተዋል። የቀድሞው የሕግ መምህር ጌታቸው ረዳ፣ በመንግሥት እና በሕወሓት መካከል በፕሪቶሪያ የሕወሓት  ዋንኛ ተደራዳሪ የነበሩ ናቸው። የሽግግር ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም እየተንቀሳቀሰች የምትገኘው ትግራይ ክልል፣ ከጦርነቱ አስቀድሞ በዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ስትመራ ነበር። ከሰሞኑ በወጡ ዘገባዎች የፌዴራሉ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትግራይ በደብረጽዮን መሪነት እንድትቀጥል አይፈልጉም። ዋሺንግተን ፖስት ይዞት በወጣው ዘገባ ዐቢይ ለትግራዩ ጦርነት መጀመር ደብረጽዮንን ይወቅሳሉ። የሕወሓት ሰዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ…
Read More