Tigray

የተመድ ፈንጅ አምካኝ ቢሮ በትግራይ ክልል ቢሮ ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ

የተመድ ፈንጅ አምካኝ ቢሮ በትግራይ ክልል ቢሮ ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ መቆሙ ይታወሳል፡፡ በዚህ ጦርነቱ ምክንያት ተቋርጠው የነበሩ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት እንዲገቡ የማድረግ ስራ በፌደራል እና ክልል መንግስታት እየተሰራም ይገኛል፡፡ ይሁንና በጦርነቱ ወቅት በየቦታው ተቀብረው የነበሩ ፈንጂዎች ትምህርትን እና ሌሎች አገልግሎቶችን ማስቀጠል አልቻሉም ተብሏል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት (UNMAS ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሰሜን ኢትዮጵያ ቦታዎች ያሉ ፈንጂዎችን እና ሌሎች የጦር መሣሪያ ቅሪቶችን የማስወገድ ተልዕኮ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ፈቃድ ተሰጥቶታል ተብሏል፡፡ እንደ አፍሪካ ህብረት መግለጫ ከሆነ ፈንጂዎችና ሌሎች ያልፈነዱ የጦር መሣሪያ ቅሪቶች ጦርነት በተካሄደባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ አካባቢዎችን ከፈንጂዎች ለማጽዳት እንዲቻል፣ የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት በመሰማራት…
Read More
በትግራይ ክልል ከ3500 በላይ መምህራንና ተማሪዎች መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ከ3500 በላይ መምህራንና ተማሪዎች መገደላቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ለሁለት ዓመታት በዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በትግራይ ክልል ስላደረሰው ውድመት ግንቦት መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የአስተዳደር በደል መከላከል ዳይሬክተር አዳነ በላይ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ከ2ሺህ በላይ መምህራን እና ከ 1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች መገደላቸው ተረጋግጧል ብለዋል። ተቋሙ በሰጠው መግለጫ በትግራይ ክልል ብቻ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን በሁሉም የማበረሰብ ክፍል ላይ ጦርነቱ ውድመት ማድረሱ ተገልጿል። በዚሁ ጦርነት ምክንያት 88 በመቶ የመማሪያ ክፍሎች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ጉዳት ደርሶባቸዋል የተባለ ሲሆን 60 በመቶ የመማሪያ መፃሕፍት ደግሞ ከጥቅም ውጪ ሆነዋል ተብሏል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የጦርነቱ ዳፋ መሠረተ ልማቶቹን በማውደም እና…
Read More
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት 28 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ማድረሱ ተገለጸ

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት 28 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ማድረሱ ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም ማዕከሉን በትግራይ ክልል አድርጎ ለሁለት ዓመታት በተካሄደውና በሌሎች የተወሰኑ አካባቢዎች በነበረው ጦርነት፣ ከ1.5 ትሪሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳትና ኪሳራ በአገር ላይ መድረሱን ገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አደረገ። የገንዘብ ሚኒስቴርን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ተቋማቸው በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተካሄደው ጦርነት የደረሰውን ጉዳትና የመልሶ ግንባታ ፍላጎት የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት (Damage and Needs Assessment) ማከናወኑን ገልጸዋል ። በጥናት ግኝቱ መሠረትም ያጋጠመው አጠቃላይ ጉዳትና የኢኮኖሚ ኪሳራ በአጠቃላይ 28 ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን ተገልጿል። ለምክር ቤቱ በቀረበው ሪፖርት ላይ ከተቀመጠው መረጃ መረዳት እንደተቻለው፣ ‹‹22 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) 20.4…
Read More
በሰሜን ኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም በያዝነው ዓመት ሕዳር ወር የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል፡፡ ይሁንና የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ የሕፃናት አድን ድርጅት/ሴቭ ዘ ችልድረን አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ እንዳለው የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር ተጨማሪ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ብሏል፡፡  በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሕፃናት በላይ ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሰ 16 ኢትዮጵያውያን ሕፃናት መሃከል አንዱ ከትምህርት ገበታ መገለሉን ያሳያል ተብሏል፡፡ ይህ አሃዝ ኢትዮጵያን ከትምህርት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ቀውስ ካስተናገዱ ሃገራት አንዷ እንደሚያደርጋት ተገልጿል፡፡  በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሚገኙ…
Read More
በትግራይ ክልል ሁለት የቀድሞ ጦር መሪዎች በምክትል ፕሬዝዳንትነት ተሾሙ

በትግራይ ክልል ሁለት የቀድሞ ጦር መሪዎች በምክትል ፕሬዝዳንትነት ተሾሙ

አዲስ በተቋቋመው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ እና ጀነራል ፃድቃን ገብረተንሳይ የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሾመዋል። ይኸው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው አዲሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር 27 አባላት ያሉትን ካቢኔ ይፋ ባደረገበት ወቅት ተገልጿል። በአዲሱ ካቢኔ ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የሰላም እና ጸጥታ ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ሆነው ሲሾሙ፣ ሌተናል ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ደግሞ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደር እና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ ሆነዋል። ሹመቱ በመቐለ ከተማ ይፋ ሲደረግ የክልሉን መንግስት ሲመራ የነበረው የቀድሞ ካቢኔ፤ የአስፈጻሚነት ስልጣኑን በጊዜያዊ አስተዳደሩ ለተቋቋመው አዲሱ ካቢኔ አስረክቧል። አዲሱ ካቢኔ የተዋቀረው ከህወሓት፣ ከትግራይ ኃይሎች፣ ከምሁራን እና ከብሔራዊ…
Read More
የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና መኮንኖች ኢትዮጵያን ጎበኙ

የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦር አመራር መኮንኖች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል። ኤርትራ ወታደራዊ ልኡክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዓቅም እና እየተከናወኑ ያሉ የምርምር እና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና፤ ኢንስቲትዩቱ እያከናወናቸው ባሉ የቴክኖሎጂ ሥራዎች ዙሪያ ለቡድኑ አባላት ገለጻ ማድረጋቸውን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡ የኤርትራ የጦር ጀነራሎች እና ከፍተኛ የጦሩ አመራሮች ቡድን አስተባባሪ ጀነራል አብርሃ ካሳ፤ በኢንስቲትዩቱ ያደረጉት ጉብኝት ለአገራቸው ብዙ ልምድ የቀሰሙበት መሆኑን መናገራቸው ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በቴክኖሎጂው ዘርፍም አብረው መስራት የሚያስችላቸው እድል ስለመኖሩም የተገነዘቡበት ጉብኝት መሆኑን መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከ20 ዓመት በፊት ወደ ደም አፋሳሽ…
Read More
የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የድጎማ በጀት እንደሚልክ ገለጸ

የፌደራል መንግስት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለትግራይ ክልል የበጀት ድጎማ መልቀቅ እንደሚጀምር የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል። ለክልሉ የሚለቀቀው በጀት፤ ለሌሎች ክልሎች እንደሚደረገው ሁሉ በወራት ተከፋፍሎ የሚላክ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት ለትግራይ በጀት ለማስተላለፍ ከስምምነት ላይ መድረሱን በተመለከተ አቶ ጌታቸው ረዳ ከቀናት በፊት ተናግረው ነበር። ባለፈው ሳምንት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተሾሙት አቶ ጌታቸው፤ የፌደራል መንግስት በጀት መፍቀዱን፤ ሆኖም የገንዘብ መጠኑን በተመለከተ ግን “ገና እንነጋገራለን” ማለታቸው ይታወሳል። የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው በበኩላቸው፤ የትግራይ ክልል በጀት “የሚታወቅ” መሆኑን ገልጸዋል። የፌደራል መንግስት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እስኪቋቋም የበጀት ድጎማ ሳይለቅቅ ቢቆይም፤ በክልሉ ውስጥ…
Read More
መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ።

መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ።

መንግሥት በህወሀት አመራሮች ላይ የመሰረተውን ክስ አቋረጠ። የፍትህ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ በፌዴራል መንግስት እና በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መሃከል በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት ከግጭቱ ጋር ተያያዥ የሆኑ ወንጀሎች ተጠያቂነት በተመለከተ ያለውን ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ ሊታዩ እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብላል። በመሆኑም በወንጀል ተጠርጥረዉ ክስ ቀርቦባቸዉ የነበሩ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮችን ክስ ማቋረጡን ሚንስቴሩ አስታውቃል። ክሱ የተቋረጠላቸው ተከሳሾች ጉዳያቸዉ በቀጣይ በሽግግር ፍትህ ማዕቀፍ እንደሚታይም ተገልጿል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ቀርቦ በክርክር ሂደት ላይ ይገኙ የነበሩ የወንጀል ክሶች በአዋጅ 943/2008 አንቀጽ 6 (3) (ሠ) መሰረት መነሳታቸውን ሚንስቴሩ ገልጻል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት…
Read More
የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ

የትግራይ አህጉረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትን እንዲያከብር ቋሚ ሲኖዶስ ጠየቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከሰሞኑ በትግራይ አህጉረ ስብከት በተሰጠ መግለጫ ዙሪያ ምላሽ ሰጥታለች። ቤተ ክርስቲያኗ በመግለጫዋ እንዳለችው በጦርነቱ ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ መዋቅርና በትግራይ ክልል አህጉረ ስብከት መካከል አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱን ገልጻለች። ይህንንም ተከትሎ በጦርነቱ ምክንያት ሁሉም የባንክ ተቋማት ሥራቸውን በማቆማቸው በየጊዜው እንደሌሎች አህጉረ ስብከት ለትግራይ አህጉረ ስብከት ይላክ የነበረው በጀት መላክ አልተቻለም ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀጣይ እርምጃ ምንድን ነው? ቤተክርስቲያኗ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር በቀኖናው መሰረት መፈታቱን ገለጸችምንም እንኳን በባንክ መዘጋት ለአገልጋይ ሠራተኞች በጀት መላክ ባይቻልም የደመወዝ መክፈያ የባንክ…
Read More
ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ውስጥ ተሰረዘ

ሕወሀት በሽብርተኝነት ከተፈረጀ ከ22 ወራት በኋላ ውሳኔው ተሽሯል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል። ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል። ለሰሜኑ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረትም በፌደራል መንግስት እና በህወሓት በኩል ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል። ስምምነቱ የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ እና የሰብዓዊ እርዳታ ለተጎጂዎች እንዲቀርብ አድርጓል። ህወሓትም ታጣቂዎቹን ወደ ካምፕ በመሰብሰብ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን…
Read More