Oromia

የአውሮፓ ህብረት በአማራ እና ኦሮሚያ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት በአማራ እና ኦሮሚያ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ እንደገለጸው ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት ሙሉ ለሙሉ ወደ ነበረበት እንዲመለስ መወሰኑን ገልጿል፡፡ የህብረቱ አባል ሀገራት ውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባደረጉት ስብሰባ ህብረቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ባጋጠመው ጦርነት ምክንያት ሻክሮ የነበረው ግንኙነት መሻሻሉን አስታውቋል፡፡ በተለይም የፌደራል መንግስት እና ህወሃት በአፍሪካ ህብረት አደራዳረነት የሰላም ስምምነት መፈራረማቸውን እንደተቀበለው ህብረቱ ገልጿል፡፡ በዚህም ምክንያት የአውሮፓ ህብረት እና የኢትዮጵያ ግንኙነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ መወሰኑን አስታወቋል፡፡ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ድጋፍ እንደሚያደርግ የገለጸው ህብረቱ የተጀመረው የሽግግር ፍትህ እና ብሄራዊ ምክክር እቅድ ውጤታማ እንዲሆን ድጋፍ አደርጋለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው የፖለቲካ መካረር የጸጥታ ችግሮች መባባስ እንዲሁም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እንዳሳሰበው ጠቅሷል፡፡…
Read More
ኢትዮጵያ ለሱዳን 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደምትልክ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሱዳን 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደምትልክ ገለጸች

ኢትዮጵያ 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ ለሱዳን ለመላክ መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ በ”ኢትዮጵያ ኤይድ” በኩል የሚቀርበው ድጋፍ በርካታ መድሃኒቶችንም እንደሚያካትት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል ። ለሱዳን ህዝብ በአሁኑ ወቅት የሚያስፈልገውን ድጋፍ ከማቅረብ ባሻገር ተፋላሚዎቹን ወገኖች ለመሸምገልም ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳላት አንስተዋል። ለሱዳን ጦር መሪ ጀነራል አልቡርሃን እና ለፈጥኖ ደራሽ ሃይል (አርኤስኤፍ) አዛዡ ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎም በድጋሚ ለንግግር ቦታ እንዲሰጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰሜኑ ጦርነት በድርድር እንዲቆም ላደረጉ አካላት እውቅና ሲሰጡ ነው ጥሪውን ያቀረቡት። የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በሽብርተኝነት ከተፈረጀው የኦሮሚያ ነጻ አውጭ ሰራዊት ጋር ድርድር እንደሚደረግ ተናግረዋል ። ድርድሩ በታንዛኒያ የሚካሄድ ሲሆን ኖርዌይ እና ኬንያ አደራዳሪዎች ይሆናሉ ተብሏል።
Read More
ሸራተን ሆቴል በጅማ ከተማ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል ሊገነባ ነው

ሸራተን ሆቴል በጅማ ከተማ ባለ አምስት ኮኮብ ሆቴል ሊገነባ ነው

በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር ያለው ሸራተን ሆቴል በ ጅማ ከተማ በፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ደረጃ ባለ አምስት ኮከብ ኢንተርናሽናል ሆቴል ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል:: የግንባታ መሰረተ ድንጋዩን የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ አስቀምጠዋል፡፡ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከዚህ በፊት ጅማ ከተማ ኖክ ማደያ አካባቢ ለመገንባት አቅዶ የነበረውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ዘመናዊ ሆቴል ወደ ከተማዋ መግቢያ እንዲዛወር ተደርጓል። ከዚህ በፊት ሆቴሉ ሊገነባበት የነበረው ቦታ ላይም ዘመናዊ የገበያ ማዕከል እንደሚገነባም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ኩባንያ አቶ ጀማል አህመድ ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በኦሮሚያ ክልል ሰፊ…
Read More
መንግሥት የአማራ ልዩ ሀይልን ጨምሮ የሁሉንም ክልል ልዩ ሀይሎች ትጥቅ እያስፈታ መሆኑን ገለጸ

መንግሥት የአማራ ልዩ ሀይልን ጨምሮ የሁሉንም ክልል ልዩ ሀይሎች ትጥቅ እያስፈታ መሆኑን ገለጸ

መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት አቅጣጫ ማስቀመጡን ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ገልጿል። በዚህ መሠረት የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ መጀመሩን አሳውቋል። በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላት እንደ ምርጫቸውና እንደ ፍላጎታቸው ፣በመከላከያ፣ በፌደራል ፖሊስ፣በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ ብሏል። በዚህ ሐሳብ ላይም ከልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ጋር ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልጿል። ቀደም ብሎም በሁሉም ክልል አመራሮች ጥናት ተደርጎበት፣ በተገኘው ውጤት ያለምንም ልዩነት ውሳኔው ስምምነት ተደርሶበታል ሲል አስታውሷል። የክልል ልዩ ኃይልን በተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች የማካተት ውሳኔና የተግባር እንቅስቃሴ በጥናት ላይ ተመሥርቶ የሚከናወን ነው ያለው መንግስት " ይህ…
Read More
በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚቃወም እና የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚቃወም እና የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን የመጡበትን ቀን በድጋፍ ሰልፍ ሲያከብሩ በአማራ ክልል ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን የመጡባትን ቀን መከራ እና ሞት እንጂ ለውጥ አላመጣልንም ሲሉ በሰላማዊ ሰልፍ ላይ ገልጸዋል፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት በህወሃት የበላይነት ይመራ የነበረው ኢህአዴግ ህዝባዊ ተቃውሞ መበርታቱን ተከትሎ ነበር የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ሀይለማርያም ደሳለኝ መጋቢት 2010 ዓ.ም ስልጣን የለቀቁት፡፡ ይህን ተከትሎም አብይ አህመድ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን ተክተው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ሹመቱን በተቀበሉበት ወቅት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ የበርካቶችን ድጋፍ እና አድናቆት ያገኙ ቢሆንም በሁለት ዓመት ውስጥ ግን ድጋፋቸው አሽቆልቁሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለይም…
Read More
የኦሮሚያ ክልል ያለበቂ ማጣራት ህጋዊ ቤቶችን እያፈረሰ እንደሆነ ኢሰመኮ ገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ያለበቂ ማጣራት ህጋዊ ቤቶችን እያፈረሰ እንደሆነ ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ የኦሮሚያ ክልል ውስጥ በቅርቡ በአዲስ መልክ በተደራጀው የሸገር ከተማ አስተዳደር የቤቶች ፈረሳ እና በግዳጅ ማስነሳት እየተከናወነባቸው ባሉ አካባቢዎች ምርመራ ማካሄዱን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ምርመራ ካደረገባቸው አካባቢዎች መካከል ቡራዩ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ መነ አብቹ እና በዙሪያው የሚገኙ አካባቢዎች ዋነኞቹ ናቸው። ቤቶቻቸው የፈረሱባቸው ሰዎች በግል እና በቡድን ለኮሚሽኑ ያቀረቡትን አቤቱታ ተከትሎ ከየካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል። ለኮሚሽኑ ቅሬታ ያቀረቡ ሰዎችን፣ የሚመለከታቸውን የከተማ አስተዳደር እና የጸጥታ አካላት በማነጋገር፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ቤቶችን የማፍረስ እና በግዳጅ የማስነሳት ሂደቱ የሚከናወንበትን ሁኔታ እንዲሁም ቀደም ሲል የፈረሱ ቤቶችን የመስክ ምልከታ በማድረግ መረጃ እና ማስረጃ ሰብስቤያለሁም ብሏል። ለኢሰመኮ ቅሬታቸውን ያቀረቡት ሰዎች ለኮሚሽኑ ሲያስረዱ በየአካባቢው ከቀድሞ/ነባር ባለ ይዞታዎች ቦታ ወይም ቤት በመግዛት ኑሮ…
Read More
የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በታጣቂዎች ተገደሉ

የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በታጣቂዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን የነቀምቴ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር በታጣቂዎች መገደላቸው ተገለፀ። የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃ ዛሬ ጠዋት በመኖሪያ ቤታቸው በር ላይ መሳሪያ በታጠቁ ሰዎች መገደላቸውን የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት አስታውቋል። ኃላፊው ወደ ስራ ለመሄድ ከቤታቸው በወጡበት ጊዜ በተተኮሰባቸው ጥይት እንደተገደሉም ነው የከተማ አስተዳደሩ ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት በማህበራዊ ገጽ ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው። አቶ ደሳለኝ ቦኮንጃ የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ከመሾማቸው አስቀድሞ የነቀምቴ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊነትን ጨም በተለያዩ ስፍራዎች ላይ ሲያገለግሉ መቆየታቸውም ተገልጿል። የነቀምቴ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ…
Read More
በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ታግተዋል ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ከ100 በላይ ሰዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መታገታቸውን የታጋቾች ቤተሰቦችና ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡  ታጣቂዎቹ ነዋሪዎችን ማገትና ማፈናቀል ከጀመሩ ረዥም ጊዜያት ቢቆጠሩም፣ በ2015 ግን ለተወሰኑ ወራት ፋታ አግኝቶ እንደነበር፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እንደ አዲስ እንደተቀሰቀሰና በዚህም ነዋሪዎቹ እየታገቱ፣ እየተፈናቀሉና ቤት እየተቃጠለ ነው ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር የነበሩ የደራ ወረዳ ሰባት ቀበሌዎችን ከሁለት ወራት በፊት በተደረገ ዘመቻ ነፃ ማድረግ ተችሎ እንደነበር ያስረዱት ነዋሪዎቹ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ግን ጥቃት ማገርሸቱን አክለው ገልጸዋል፡፡ ጋዜጣው በስልክ አነጋገርኳቸው ያላቸው አምስት የወረዳው ነዋሪዎች እንደገለጹት፣ የአካባቢው ነዋሪዎች በታጣቂ ቡድኑ እየተሰቃዩ መሆናቸውን፣ በርካታ ሰዎች በየቀኑ እየታገቱና እየተፈናቀሉ እንደሆኑ፣ የታገቱ…
Read More
በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙ ጳጳሳት አህጉረ ስብከቶችን መልቀቃቸው ተገለጸ

በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙ ጳጳሳት አህጉረ ስብከቶችን መልቀቃቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አገረ ስብከት በሦስት አባቶች ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ በሆነ መልኩ ለ25 አባቶች ሕገ ወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት መሰጠቱ አይዘነጋም፡፡ ይህን ተከትሎም ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 18 ቀን 2015 በጠራው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባዔ፣ እነዚህን አካላት ከቤተክርስቲያን ሕብረት ለይቶ ማውገዙ፣ እንዲሁም በየትኛውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ እንዳይገኙ የእግድ ውሳኔ አሳልፎ ነበር፡፡ ችግሩ በእርቅ ለመፍታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኩል በተደረገው ስምምነት መሰረት፣ በሹመቱ የተካተቱ አካላት ወደ ቀድሞ ሥማቸው እንዲመለሱ ስምምነት ከተደረገ በኋላም፤ ጉዳዩ በስምምነቱ መሰረት አለመፈጸሙን ቤተክርሰውቲያኗ በተደጋጋሚ ገልጻለች፡፡ ሕገ ወጥ የተባሉት ተሹዋሚዎች ከስምምነቱና ከሲኖዶስ ውሳኔ አፈንግጠው፣ ኦሮሚያ ውስጥ በሚገኙ አህጉረ ስብከቶች በተለይም በወለጋ…
Read More