EthioNegari

አሜሪካ ኤርትራን ጨምሮ በ10 ሀገራት ያሏትን ኢምባሲዎች ልዘጋ ነው

አሜሪካ ኤርትራን ጨምሮ በ10 ሀገራት ያሏትን ኢምባሲዎች ልዘጋ ነው

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር መንግስት ወጪ ቅነሳ ላይ ሲሆን አሁን ደግሞ ኢምባሲዎችን ለመዝጋት ማሰባቸው ተገልጿል፡፡ ፖለቲኮ እንደዘገበው ከሆነ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የወጪ ቅነሳ አዲስ እቅድ አውጥቷል፡፡ በዚህ እቅድ መሰረትም የመስሪያ ቤቱን አመታዊ ወጪ በግማሽ በመቶ ለመቀነስ መታሰቡ ተገልጿል፡፡ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ ከቀረቡ  ምክረ ሀሳቦች መካከል በዓለም ላይ ያሉ የአሜሪካ ኢምባሲዎች እና ቆንሱላ ጽህፈት ቤቶችን ለመዝጋት ታቅዷል ተብሏል፡፡ በዓለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ ኢለን መስክ ምክር የሚመራው የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር መንግስት አሁን ደግሞ ትኩረቱን ወደ ኢምባሲዎች መዝጋት አዙሯል፡፡ ከቀረቡት ምክረ ሀሳቦች ውስጥ 10 የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና 17 ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችን ለመዝጋት መታቀዱ ተገልጿል፡፡ በእቅድ ደረጃ እንዲዘጉ ከተባሉት ኤምባሲዎች እና…
Read More
በኢትዮጵያ ተማሪዎች ስልክ ወደ ትምህርት ይዘው እንዳይገቡ ሊከለከሉ ነዉ

በኢትዮጵያ ተማሪዎች ስልክ ወደ ትምህርት ይዘው እንዳይገቡ ሊከለከሉ ነዉ

ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስልክ ይዘው እንዳይሄዱ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል መጀመሩን የትምህርት ሚንስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስልክ የሚባል ነገር ይዘው እንዳይገቡ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በሚመሩት የትምህርት ዘርፍ ላይ ስለ አፈጻጻምና ስለታቀዱ እቅዶች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በሰጡት ማብራሪያም በሚቀጥለው ሳምንት ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር ውይይት እንደሚካሄድ ጠቁመዋል። በዚህም ወቅት ተማሪዎች ስልክ ትምህርት ቤት ይዘው እንዳይገቡ ለማድረግ ስለሚደረገው እንቅስቃሴ እንደሚመከር ገልጸዋል። “ የጋራ ስምምነት ላይ ከደረስን ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ገብተው ትምህርት መከታተል ነው እንጂ ከስልክ ጋር የሚጫወቱበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ይደረጋል “ ብለዋል። ብተያያዘ ዜና ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ…
Read More
ኢትዮጵያ ከዩኤስኤይድ የገንዘብ ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ ድርጅቶችን መመዝገብ ጀመረች

ኢትዮጵያ ከዩኤስኤይድ የገንዘብ ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ ድርጅቶችን መመዝገብ ጀመረች

በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ስር ተመዝግበው ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) እና ከአሜሪካ መንግስት ሌሎች ተቋማት የገንዘብ ድጋፍ በመቀበል በአገሪቱ ውስጥ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውኑ የነበሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መረጃቸውን ለመንግስት እንዲያቀርቡ ተጠይቀዋል። ይህ ጥሪ የአሜሪካ አስተዳደር በአገር ውስጥም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ እያደረገ ያለውን የገንዘብ ድጋፍ መቀነስ ወይም ማቆም ጋር በተያያዘ ለቀጣይ ተግባራት አስፈላጊውን መረጃ ለመሰብሰብ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ይህን ተከትሎም USAIDን ጨምሮ ከማንኛውም የአሜሪካ መንግስት ተቋም የገንዘብ ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ ሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እስከ ሚያዝያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ሪፖርት እንዲያደርጉ ተጠይቀዋል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ማህበር መንግስት በዩኤስኤይድ ጉዳይ የዲፕሎማሲ ድጋፍ እንዲያደርግ መጠየቁ ይታወሳል። ባሳለፍነው…
Read More
በትግራይ ክልል 259 ሰዎች በፈንጅ መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል 259 ሰዎች በፈንጅ መገደላቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ባለፈው ሁለት አመት 1664 ሰዎች በተቀበሩ ፈንጂዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል፡፡ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈፀመ ወዲህ ይህንን ያህል ቁጥር ያላቸው ሰዎች ጉዳት ሲደርስባቸው ከእነዚህ ውስጥ 259ኙ ደግሞ ህይወታቸው እንዳለፈ የክልሉ መልሶ ግንባታና ልማት ድርጅት (ራዶ) አስታውቋል፡፡ አለም አቀፍ የፈንጂ ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቀሌ በተደረገ ስብሰባ ላይ የክልሉ መልሶ ግንባታና ልማት ድርጅት ሀላፊው አቶ ተስፋይ ገብረማሪያም እንደገለፁት የተቀበሩ ፈንጂዎችና ጥይቶች አሁንም በተለያዩ የትግራይ ክፍሎች ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የፈንጂ አምካኝ ግብረ ሀይል አስተባባሪ የሆኑት ኮሎኔል ተስፋይ አብርሀ በበኩላቸው በክልሉ ውስጥ በየቀኑ የፈንጂ አደጋዎች እየደረሱ መሆናቸውን ገልፀው የበጀት እጥረትና ለጉዳዩ በቂ ትኩረት አለመስጠት ስራቸውን እያደናቀፈባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ላለፉት ሁለት ዓመታት ትግራይን…
Read More
የአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ተጠናቀቀ

የአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ተጠናቀቀ

የአማራ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ሲያካሄዱት የቆየው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቋል፡፡ የአማራ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ካለፈው እሁድ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲያካሄዱት የቆየው የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት መጠናቁን ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የማህበረሰብ ተወካዮቹ፤ በመጪዎቹ ቀናት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በሚደረግ የምክክር ሂደት የሚሳተፉ 270 ወኪሎቻቸውንም መርጠዋል። በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር በተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ከ263 ወረዳዎች የተመረጡ ከ4,500 በላይ የሚሆኑት የማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ አስር የማህበረሰብ ክፍሎችን የወከሉት እነዚህ የሀገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች፤ በባህርዳር ከተማ በነበራቸው ቆይታ ከዘጠኝ እስከ 12 አባላት በሚገኙባቸው ቡድኖች ተከፋፍለው በአበይት ክልላዊ እና ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ሲወያዩ ቆይተዋል። ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አስመረቀ

ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አስመረቀ

ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ ከመገናኛ ወደ ቦሌ  በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ እጅግ ፈጣን ያለውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ሁለተኛውን ጣቢያ በይፋ ሥራ አስጀምሬያለሁ ብሏል። ኩባንያው ከዚህ ቀደም ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ 16 መኪኖችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚችል የኤሌክትሪክ መኪና መሙያዎችን የያዘ ጣቢያ ገንብቼ ወደ ስራ አስገብቻለሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም ከየካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ14 ሺህ 280 የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎት መስጠት ችሏል ተብሏል። ለዚህም 376,574.72 ኪሎዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥቅም ላይ ውሏል የተባለ ሲሆን በተጨማሪም 521,074.23 ኪሎግራም ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ መከላከል የተቻለ ሲሆን፣ ይህም ከ2,622 በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እንደሚነጻጸር ተገልጿል። በምራፍ ሁለት…
Read More
ጀነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነው ተሾሙ

ጀነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነው ተሾሙ

የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ከተመሰረተ በኃላ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ረዳ ምክትል በመሆንና የሰላምና ፀጥታ ካቢኔ ሲክሬተርያት ሀላፊ ብሎም የትግራይ ጦር አዛዥ በመሆን ሲሰሩ የቆዩት ጀነራል ታደሰ በዛሬው እለት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነው ተሾመዋል። ጀነራል ታደሰ ቀደም ሲል በህወሓት አቶ ጌታቸውን በመተካት ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ ተመርጠው ፌደራል መንግስትም ይህንኑ የህወሓት ምርጫ ተቀብሎት እንደነበር ከዚህ ቀደም ፓርቲው ማስታወቁ አይዘነጋም። ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን የተረከቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ሚኒስትሮች፣ ተጋባዥ እንግዶች እና ሌሎች አካላት በስልጣን ርክክቡ ላይ ተገኝተዋል፡፡ ጀነራል ታደሰ ወረደ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስ፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሠረት ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ መልሶ…
Read More
የጥላቻ ንግግሮች የኢትዮጲያ ሴቶችን ከማህበራዊ ተሳትፎ እየገደበ ነው ተባለ

የጥላቻ ንግግሮች የኢትዮጲያ ሴቶችን ከማህበራዊ ተሳትፎ እየገደበ ነው ተባለ

ኢትዮጲያ ውስጥ ሴቶች እና ልጃገረዶች ከማህበራዊ ኑሮ እየተገለሉ እና በማህበራዊ ትሥሥር ድረ-ገፆች ላይም በተደጋጋሚ መገፋት እና ማጥላላት እየደረሰባቸዉ ነዉ። እነዚህ ግኝቶች ሴንተር ፎር ኢንፎርሜሽን ሪዚሊየንስ (ሲ.አይ.አር) በተባለ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን፣ የሀሰት መረጃን እና ኢንተርኔት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን መከላከል ላይ አተኩሮ በሚሰራ ገለልተኛና ለትርፍ ባልተቋቋመ ተቋም በተደረጉ ጥናቶች የተገኙ ናቸው። ይህ ጥናት ሲ.አይ.አር ኢትዮጲያ ውስጥ በፌስቡክ፣ ኤክስ (X) እና ቴሌግራም ላይ የሚፈጸሙ ጾታን መሰረት ያደረጉ ትንኮሳዎች ላይ ቀደም ብሎ ያደረገውን ጥናት ወደ ሁለት ተጫማሪ የማህበራዊ ትሥሥር ድረ-ገፆች ማለትም ዩትዩብና ቲክቶክ አስፋፍቷል። ግኝቶቹም እንደሚያሳዩት በማህበራዊ ትሥሥር ድረገፆች ላይ የሚደረጉ የጥላቻ ንግግሮች የሰዎችን የመናገር፣ የመምራት እና በዲጂታሉ አለም ያላቸውን ደህንነት እየገደበ እንዳለና እና…
Read More
የእስራኤል አምባሳደር ከአፍሪካ ህብረት ተባረሩ

የእስራኤል አምባሳደር ከአፍሪካ ህብረት ተባረሩ

የእስራኤል አምባሳደር ከሩዋንዳ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ ላይ በአፍሪካ ህብረት ተባረሩ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር የሆኑት አብርሃም ንጉሴ፣ ዛሬ መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም. በሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ሰለባዎችን ለማስታወስ በተካሄደው 31ኛዉ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ከአፍሪካ ህብረት ዋና ጽህፈት ቤት እንዲወጡ ተደርጓል። ይህ የሆነው በርካታ የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት አምባሳደሩ በዚሁ የሐዘን ስነ-ስርዓት ላይ መገኘታቸውን በመቃወማቸው መሆኑ ተዘግቧል ። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኦረን ማርሞርስቴይን ድርጊቱን "አሳፋሪ" እና "ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ በጽኑ አውግዘዋል። "በአዲስ አበባ የሚገኘው የእስራኤል አምባሳደር በተጋበዙበት፣ በሩዋንዳ የቱትሲ የዘር ማጥፋት ሰለባዎችን ለማስታወስ በተዘጋጀ ዝግጅት ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ፀረ-እስራኤላዊ የፖለቲካ አመለካከቶችን ማስተዋወቃቸው እጅግ አሳፋሪ ነው" ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ማርሞርስቴይን…
Read More
ኢትዮጵያ በውጭ ባንኮች ላይ የአምስት ቢሊዮን ብር ግዴታ ጣለች

ኢትዮጵያ በውጭ ባንኮች ላይ የአምስት ቢሊዮን ብር ግዴታ ጣለች

ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጪ ባንኮች አምስት ቢሊዮን ብር ዝቅተኛ ካፒታል ሟሟላት እንደሚኖርባቸው ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ ጥብቅ ቅደመ ሁኔታዎችን ያስቀመጠ ነው ተብሏል። መመሪያው በባንኩ ዘርፍ የውጭ ሀገራት ተሳትፎን የውጭ ባንክ ተቀጥላ፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፍ እና የእንደራሴ ቢሮ ብሎ የሚከፍል ሲሆን ወደ ሥራ ከመግባታቸው በፊት የወንጀል እና የታክስ ማጣራትን ጨምሮ ጥብቅ ምርምራዎችን ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው አስቀምጧል። የውጭ ባንኮች የደንበኞቻቸውን መረጃ በኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ ብቻ ለማስቀመጥ እና ለመጠቀም ይገደዳሉ የተባለ ሲሆን ክፍያን በተመለከተ ከውጭ የሚገቡ ባንኮች ለምርመራ 200 ሺህ፣ ለፈቃድ 400 ሺህ እና ለእድሳት 400 ሺህ ብር መክፈል እንዳለባቸው ተቀምጧል። መመሪያው የሀገር ውስጥ ባንኮች ካፒታላቸውን መጨመር፣ የመረጃ አጠቃቀም ሕጋቸውን ከሀገሪቱ…
Read More