amharanews

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 30 ንጹሃን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 30 ንጹሃን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃ እና ወደራ ወረዳ ሳሲት በተባለች ከተማ ህዝብ ያሳፈረ አይሱዙ ተሽከርካሪ ላይ በተፈጸመው ጥቃት 30 ሰዎች ሲገደሉ 18 ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ከአምስት ቀን በፊት ሳሲት በተባለችው ከተማ አቅራቢያ 50 ሰዎችን ያሳፈረ አይሱዙ ተሽከርካሪ መንገደኞችን ለማውረድ በቆመበት ተፈጽሟል በተባለው ጥቃት 18 ሰዎች መቁሰላቸውንም ነው የአይን እማኞችን የጠቀሰው የሪሊፍ ዌብ ዘገባ የሚያሳየው። የድሮን ጥቃቱ ሲፈጸም በአካባቢው በመከላከያ ሰራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት እንዳልነበር የተናገሩት ነዋሪዎች፥ ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላም ድሮኖች በአካባቢው ሲሽከርከሩ እንደነበር ገልጸዋል። የድሮን ጥቃቱ የተፈጸመው መከላከያ ሰራዊት እና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ ከሚያደርጉበት አካባቢ በ24 ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንደተፈጸመ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ “መጀመሪያ ከባድ ፍንዳታ ሰማን ከዚያም…
Read More
በደላንታ ኦፓል በማውጣት ላይ እያሉ የተቀበሩ 20 ወጣቶችን ለማትረፍ ህዝቡ ሌት ተቀን እየቆፈረ ነው ተባለ

በደላንታ ኦፓል በማውጣት ላይ እያሉ የተቀበሩ 20 ወጣቶችን ለማትረፍ ህዝቡ ሌት ተቀን እየቆፈረ ነው ተባለ

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ 018 ቀበሌ ልዩ ስሙ አለኋት ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ነበር ኦፓል ማዕድን በማውጣት ላይ የነበሩ ወጣቶች መውጫ ስፍራ በአለት የተደፈነባቸው፡፡ በማህበር ተደራጅተው ኦፓል እንዲያወጡ የተደራጁት እነዚህ ወጣቶች ቁጥራቸው 20 ሲሆን ከመሩት በህይወት ለማትረፍ የአካባቢው ማህበረሰብ ሌት ተቀን በፈረቃ እየቆፈረ መሆኑን የዞኑ መንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ እያሱ ለአልዐይን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ እያሱ ገለጻ ከሆነ ወጣቶቹ ሌሊት ላይ ማዕድኑን ለማውጣት እየቆፈሩ እያሉ መውጫቸው በዓለት የተዘጋ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ በተመሳሳይ ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ጉዳዩን ለህዝብ አሳውቀዋል፡፡ ጥር 30 ቀን የተከሰተው ይህ አደጋ ከመሬት ውስጥ ባለው ዋሻ ውስጥ ያሉትን ወጣቶች የደላንታ ወረዳ እና የአካባቢው ማህበረሰብ በዘመቻ…
Read More
አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ባሳለፍነው ሳምንት ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢምባሲው ማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ባወጡት መግለጫ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ዜጎች ግድያ እንደሚያሳስባቸው፣ ጉዳዩ በገለልተኛ አካል እንዲመረመር ጠይቀዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ እና ኦሮሚያ…
Read More
ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ 10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ 10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈሏ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት በመሻሻል ላይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመንግስታቸውን የስድስት ወራት አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሌት “ህገ መንግስት ጋር ተያይዞ ከአማራ ክልል ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሟል፤ ስራውን እየሰራ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የአማራ ህዝብ በስራ ላይ ባለው ሕገ መንግስት ምክንያት ተንቀሳቅሶ መስራት፣ ሀብት ማፍራት ሌሎች የማንነት ጥያቄዎች እንዳይፈቱ አድርጓል የሚል ጥያቄ አላቸው፡፡ በዚህም መሰረት የአማራ ህዝብ ይህ በስራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ሲዘጋጅ እና ሲጸድቅ በቂ ውይይት እንዳልተደረገበት እንዲሁም የአማራ ህዝብን አግላይ ነው በሚል ጥያቄዎችን ሲያነሱ ቆይተዋል፡፡ ለአብነትም የአማራ ክልል ወሰን አከላለል ትክክል…
Read More
ኢትዮጵያ ከቆዳ እና ማዕድናት ንግድ 200 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከቆዳ እና ማዕድናት ንግድ 200 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

በ2016 በጀት ዓመት ሥድስት ወራት 100 ሚሊየን ዶላር ማጣቱን የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር አስታውቋል። የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፀሐፊ እንዳለ ሰይፉ፥ ባለፉት ሥድስት ወራት 124 ሚሊየን ዶላር ከቆዳ ምርቶች ሽያጭ ለማግኘት ታቅዶ መሰራቱን ተናግረዋል። ይሁን እንጅ ማሳካት የተቻለው 14 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላር ብቻ መሆኑን ተናግረው በግማሽ ዓመቱ የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ቅናሽ አሳይቷል። የቆዳ ዘርፉ ከ2010 ዓ.ም በኋላ ባሉት ተከታታይ ዓመታት ከፍተኛ የገቢ ማሽቆልቆል እንዳጋጠመውም አስረድተዋል። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የሥራ ማስኬጃ በጀት እጦትና ለዘርፉ የተሰጠው የትኩረት ማነስ ለገቢው መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያትም የቆዳ ፋብሪካዎች ከሥራ…
Read More
ኢትዮጵያ ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ጦሯ ዝግጁ መሆኑን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ጦሯ ዝግጁ መሆኑን ገለጸች

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፎልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዳሉት ሰራዊቱ “ከየትኛውም አቅጣጫ የሚሰነዘርበትን ጥቃት” ለመመከት ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡ ዋና አዛዡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ለ24ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን መኮንኖች ባስመረቀበት ወቅት እንዳሉት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ወቅት “በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት ጥረት እያደረገች ያለችበት ነው” ያሉት አዛዡ የሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች የውስጥ ችግሮችን ለማባባስ “የቋመጡበት እና የቆረጡበት” ወቅት እንደሆነም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ “ከቀይ ባህር ተገፍታ በመቆየቷ የደረሰባትን የኢኮኖሚና የጸጥታ ተግዳሮቶችን እና ስብራቶችን” ለመቅረፍ “እየሞከረች” ያለችበት መሆኑን ልብ ሊሉት እንደሚገባ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ለተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖቹ አሳስበዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ…
Read More
በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች በመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ

በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች በመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በአማራ ክልል በርካታ አካባቢዎች ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ሲሆን የፋኖ ታጣቂዎች በተለይም የገጠር አካባቢዎችን ተቆጣጥረው ሲያዙ ከተሞች ደግሞ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተይዘዋል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት…
Read More
በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል ባሳለፍነው ነሀሴ ለስድስት ወራት የታወጀው አስቸኳይ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት ተራዝሟል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባ በአማራ ክልል የታወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት  አራዝሟል። የምክር ቤቱ አባላት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዙሪያ አደረጉት በተባለው ውይይት ከዋጁ በሁለት ተቃውሞ በሶሰት ድምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ለአራት ወራት እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት ወስኛለሁ ማለቱን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው፡፡ ይህ ግጭት ቀስ በቀስ እያደገ መጥቶ ወደ ጦርነት የተቀየረ ሲሆን የቀድሞው የክልሉ መንግስት በመደበኛ…
Read More
አቶ ደመቀ መኮንን ከስልጣን ለቀቁ

አቶ ደመቀ መኮንን ከስልጣን ለቀቁ

የኢትዮጵያ ገዢ የሆነው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ደመቀ መኮንን ከስልጣናቸው ለቀቁ፡፡  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ደመቀ መኮንን ከፓርቲ ኃላፊነታቸው መሸኘታቸውን ፓርቲያቸው አስታውቋል። የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ " የአመራር የመተካካት መርኅን እና የአሠራር ሥርዓት በመከተል አቶ ደመቀን በክብር ተሸኝተዋል " ሲል ገልጿል። አቶ ደመቀን መኮንንን በመተካት የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እና የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባል አቶ ተመስገን ጥሩነህ የብልጽግና ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል። አቶ ደመቀ ከፓርቲው አመራርነታቸው መሰናበት በአገሪቱን መንግሥት ውስጥ ይዘው ከሚገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቦታን ሊለቁ እንደሚችሉ አመላካች መሆኑ ተነግሯል። አቶ ደመቀ የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነትና…
Read More
በኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት 21 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች መዘግየታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በጦርነት ምክንያት 21 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች መዘግየታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለመስራት ካቀዳቸዉ 54 የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዉስጥ 21 ያህሉን በጸጥታ ችግር መተግበር እንዳልቻለ አስታወቀ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የ 2016 አመት ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርትን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አቅርበዋል። አስተዳደሩ በወራቱ ለማከወን ካከቀዳቸዉ 54 ፕሮጀክቶች ዉስጥ 21 ያህሉን በጸጥታ ችግር መተግበር እንዳልቻለ ዋና ዳይሬክተሩ ለቋሚ ኮሚቴዉ ተናግረዋል። በዚህም በስድስቱ ወራት የነበረዉ የዲዛይን ስራዎች አፈጻጸም 57 በመቶ ሲሆን ይህም ዝቅተኛ እንዲሆን እንዳደረገበት ለምክር ቤቱ ገልጸዋል። በተጨማሪም በዉጭ አማካሪ ድርጅት ለተሰራ ስራ ክፍያ የዉጭ ምንዛሪ በመዘግየቱ የተጓተቱ ፕሮጀክቶች መኖራቸዉንም ዋና ዳይሬክተሩ አንስተዋል። በተለያዩ ምክኒያቶችም 84 ፕሮጀክቶች መቋረጣቸዉ እና ሙሉ በሙሉ የኮንትራት ዉላቸዉ መሰረዙንም…
Read More