amharanews

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በመከታተል እና ሪፖርቶችን በማውጣት የሚታወቀው ኔት ብሎክስ የ2023 ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ ተቋም ሪፖርት መሰረት ኢትዮጵያ ከኢንተርኔት በመዝጋት ገቢ ካጡ ሀገራት መካከል ከሩሲያ በመቀጠል ከፍተኛ ገቢ ያጣች ሀገር ተብላለች፡፡ ሩሲያ 113 ሚሊዮን ዜጎቿን ከኢንተርኔት ውጪ በማድረጓ አራት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ስታጣ ኢትዮጵያ ደግሞ 30 ሚሊዮን ገደማ ዜጎች ከኢንተርኔት አገልግሎት ውጪ ተደርገዋል፡፡ ሆን ተብሎ በመንግስት እንደተወሰደ የተገለጸው ይህ ኢንተርኔት ማቋረጥ ኢትዮጵያ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አሳጥቷታል ተብሏል፡፡ ሀገራት ኢንተርኔት አገልግሎቶችን የሚያቋርጡት በሶስት ምክንያት ነው የተባለ ሲሆን ተቃውሞዎችን ለማፈን፣ የሀሳብ ነጻነትን ለመገደብ እና የምርጫ ስራዎች እንዳይታወኩ በሚል እንደሆነም ተገልጿል፡፡ 25 የዓለማችን ሀገራት ኢንተርኔት አቋርጠዋል የተባለ ሲሆን…
Read More
በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

የፍትህ ሚኒስቴር በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ ባሉ 52 ተጠርጣሪዎች ላይ የፖለቲካ ርዕዮትን በሀይል ለማስፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀል ህግ እንዲሁም የሽብር ወንጀሎችን ለመከላከል የወጣውን ህግ ጥሰዋል በሚል ክስ መስርቷል፡፡ በዚህ ክስ መዝገብ ስርም ክርስቲያን ታደለ፣ ዮሀንስ ቧያለው፣ ካሳ ተሸገር (ዶ/ር) ጫኔ ከበደ፣ እስክንድር ነጋ፣ ዘመነ ካሴ፣ አበበ ፈንታው፣ አሰግድ መኮንን፣ መከታው ማሞ፣ ፈንታሁን ሙሃባ እና ሌሎችም ተካተዋል፡፡ ከ52ቱ ተከሳሾች መካከል 14ቱ ተጠርጣሪዎች ልደታ በሚገኘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀሎች ችሎት የቀረቡ ሲሆን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ እና ቤተሰቦች መገኘታቸው ተገልጿል፡፡ የተጠርጣሪዎች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአልዐይን እንዳሉት በችሎቱ መገኘታቸውን ገልጸው ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ማንነት ካረጋገጠ በኋላ የተለያዩ ትዕዛዞችን…
Read More
በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት ከስድስት ሺሕ በላይ ሠራተኞች ሥራ ማቆማቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት ከስድስት ሺሕ በላይ ሠራተኞች ሥራ ማቆማቸው ተገለጸ

ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት ወስኛለሁ ማለቱን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው፡፡ ይህ ግጭት ቀስ በቀስ እያደገ መጥቶ ወደ ጦርነት የተቀየረ ሲሆን የቀድሞው የክልሉ መንግስት በመደበኛ የክልሉ የጸጥታ ሀይል ህግ ማስከበር እንደማይችል እና የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ በደብዳቤ ጠይቋል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሀምሌ 2015 ዓ.ም መጨረሻ ቀናት ጀምሮ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ የነበረ ሲሆን አዋጁ ለተጨማሪ አራት ወራት መራዘሙ አይዘነጋም፡፡ በዚህ ጦርነት ምክንትም ከስድስት ሺህ በላይ የሆኑ ሰራተኞች ስራ ማቆም እና ቤተሰቦቻቸውን መመገብ አለመቻላቸው ተገልጿል፡፡ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ከሥራ ውጭ የኾኑ ዜጎች፣ በግጭቱ ምክንያት…
Read More
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ጀነራል ክንፈ ዳኘው እና አብዲ ኢሌ ከእስር ተፈቱ

ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ጀነራል ክንፈ ዳኘው እና አብዲ ኢሌ ከእስር ተፈቱ

በ2013 በተካሄደው ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በባህርዳር ከተማ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ተወዳድረው የተመረጡት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ታስረው ነበር፡፡ ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ እንዳሉት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በመታወቂያ ዋስትና ከእስር ተለቀዋል። የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ከሁለት ወራት በፊት በጸጥታ ሀይሎች ተይዘው የታሰሩ ቢሆንም ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቆይተው ዛሬ ከእስር ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸውን ጠበቃቸው ተናግረዋል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ በተመሳሳይ ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጽታ ሀይሎች ተወስደው በእስር ላይ የነበሩት ሌላኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብታቸው ከታሰሩ ከሰባት…
Read More
በእስር ላይ የነበሩት አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት ተነሳ

በእስር ላይ የነበሩት አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብት ተነሳ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባ የአቶ ክርስቲያን ታደለን ያለመከሰስ መብትን  በሁለት ተቃውሞ እና በሁለት ድምጸ ተዐቅቦ አንስቷል። አቶ ክርስቲያን ታደለ ከሶስት ዓመት በፊት በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ከቋሪት ወረዳ ተመርጠዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ሪፖርታቸውን ለምክር ቤቱ በሚያቀርቡበት ወቅት ጠንካራ ጥያቄዎችን በማንሳት እና ትችቶችን በመሰንዘር የሚታወቁት አቶ ክርስቲያን ታደለ ከስድስት ወራት በፊት ታስረዋል፡፡ ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ላለፉት ስድስት ወራት በእስር ላይ የቆዩት አቶ ክርስቲያን ታደለ በዛሬው ዕለት ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቷል፡፡ ሌላኛው የምክር ቤት አባል አቶ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ከሁለት ወራት በፊት ያለ መከሰስ መብታቸው ሳይነሳ በተመሳሳይ በእስር ላይ ያሉ ሲሆን እስካሁን ክስ ሳይመሰረትባቸው…
Read More
በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት 15 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ ንብረት መውደሙ ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት 15 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ ንብረት መውደሙ ተገለጸ

ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት ወስኛለሁ ማለቱን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው፡፡ ይህ ግጭት ቀስ በቀስ እያደገ መጥቶ ወደ ጦርነት የተቀየረ ሲሆን የቀድሞው የክልሉ መንግስት በመደበኛ የክልሉ የጸጥታ ሀይል ህግ ማስከበር እንደማይችል እና የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ በደብዳቤ ጠይቋል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሀምሌ 2015 ዓ.ም መጨረሻ ቀናት ጀምሮ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ የነበረ ሲሆን አዋጁ ለተጨማሪ አራት ወራት መራዘሙ አይዘነጋም፡፡ የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊና የኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ጣሰው በዚህ ጦርነት ዙሪያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በክልሉ እየተካሄደ…
Read More
በአማራ ክልል በጦርነት እና ድርቅ ምክንያት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል በጦርነት እና ድርቅ ምክንያት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር እና ድርቅ ምክንያት 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን በክልሉ ያለው የጸጥታ እና ድርቅ ችግሮች በተማሪዎች ምዝገባ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል ብለዋል። ክልሉ 6 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር ሲገባው ያን ማድረግ አለመቻሉን ኃላፊው ተናግረዋል። ከሁለት ነጥብ 6 ሚሊዮን ያልተመዘገቡ ተማሪዎች መኖራቸውን የገለፁት ኃላፊው ፤ መማር የሚገባቸው ተማሪዎች የትምህርት ዕድል እንዳያገኙ መደረጉን አመልክተዋል። ከ2015 ዓ/ም ሚያዚያ ወር ጀምሮ የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ አደራጃለሁ የሚል ውሳኔ ካሳለፈበት ጊዜ ጀምሮ በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል…
Read More
በባህር ዳር ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከባድ ጦርነት መከሰቱ ተገለጸ፡፡

በባህር ዳር ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከባድ ጦርነት መከሰቱ ተገለጸ፡፡

በአማራ ክልል መዲና ባህርዳር ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከባድ ተኩስ ሲካሄድ እንደነበር ነዋሪዎች ነግረውናል፡፡ ለደህንነታቸው የሰጉ እና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የባህርዳር ከተማ ነዋሪ እንዳሉን ከሆነ ከዛሬ ማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ የተኩስ ድምጽ መስማታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ነዋሪው አክለውም በፍርሃት ቤት ውስጥ በራቸውን ዘግተው ቤተሰባቸውን ይዘው መቀመጣቸውን የነገሩን እኝህ ነዋሪ በተለይም እስከ ጠዋቱ 3 ሰዓት ድረስ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ መካሄዱንም ነግረውናል፡፡ ውጊው በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል መካሄዱን እርግጠኛ ነኝ የሚሉን እኝህ ነዋሪ ንጹሃን ከቤታቸው ባለሙውጣታቸው የከፋ ጉዳት እንዳላስተናገዱም አክለዋል፡፡ አሁን ላይ በተለይም ከምሳ ሰዓት ጀምሮ የውጊያ ድምጽ እየሰሙ እንዳልሆነ አንቡላንሶች በመንገዶች ላይ ሲመላለሱ መመልከታቸውንም ነግረውናል፡፡ ሌላኛው በባህር ዳር መሀል ከተማ…
Read More
ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

በኢትዮጵያ እያሻቀበ ላለው የተረጂዎች ቁጥር ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ መንግስት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች የምግብ ርዳታ ለማቅረብ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግሥት በጋራ ባወጡት ሪፖርት ላይ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ አታለለ አቡሃይ፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው የተረጅዎች ብዛት 6 ነጥብ6 ሚሊዮን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተፈጥሮ አደጋዎች፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ጦርነት እና ሌሎች አደጋዎች ምክንያት የተፈናቃዮች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል፡፡ የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ካደረጉ በኋላ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም አሳሳቢ የምግብ…
Read More
በባህርዳር 17 ንጹሃን ዜጎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ከህግ ውጪ መገደላቸው ተገለጸ

በባህርዳር 17 ንጹሃን ዜጎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ከህግ ውጪ መገደላቸው ተገለጸ

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር ንጹሃንን ከህግ አግባብ ውጪ ገድሏል ብሏል። ተቋሙ በአማራ ክልል ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ሰፋ ያለ ሪፖርቱን አውጥቷል። በአቡነ ሃራ፣ ልደታ እና ሳባ ታሚት በተባሉ አካባቢዎች ከ17 በላይ ንጹሃን በመከላከያ ተተኩሶባቸው መገደላቸውን ከአይን እማኞች ማረጋገጡን የጠቆመው አምነስቲ ኢንተርናሽናል አንዳንድ ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው ሰዎች አስከሬን መውሰድ እና መቅበር ተከልክለዋል ተብሏል፡፡ ሪፖርቱ በአማራ ክልል የመከላከያ ሰራዊትና የፋኖ ታጣቂዎች ውጊያ እንደጀመሩና ከሶስት ወር በኋላ በባህር ዳር ተፈጸሙ የተባሉ ግድያዎችን ብቻ የቃኘ ነው። የኢንተርኔት አገልግሎት መዘጋት እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስከተላቸው ክልከላዎች በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ጦርነት የተፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በዝርዝር…
Read More