05
Aug
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ብሊንከን በዚሁ ውቅት በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው ሁኔታ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት ስጋት የሚፈጥር ነው ብለዋል። ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የእርዳታ እህል በፍትሃዊ መንገድ በሚቀርብበት መንገድ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር መክረዋል። በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችንም በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አሜሪካ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል ተብሏል። በአማራ ክልል በሀገር መከላከያ እና ፋኖ መካከል ካሳለፍነው ሚያዝያ ጀምሮ ግጭት ውስጥ ገብተዋል። ግጭቱ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን የክልሉ መንግሥት ጉዳዩ ከአቅሜ በላይ ነው ሲል የፌደራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል። በክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ መባባሱን ተከትሎ የኢትዮጵያ…