Ethiopia

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ቃል አቀባይ በቴ ኡርጌሳ ተገደሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ቃል አቀባይ በቴ ኡርጌሳ ተገደሉ

የተቃዋሚው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ፓርቲ (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር / የፖለቲካ ኦፊሰር የሆኑት አቶ በቴ ኡርጌሳ ትላንትና ለሊት በመቂ ከተማ መገደላቸው ተገልጿል። "ካረፉበት ሆቴል ውስጥ ትላንት ለሊት ተወስደው ተገድለው ነው አስክሬናቸው መንገድ ላይ ተገኝቷል" ሲል ፓርቲያቸው ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ኢነግ በመግለጫው አክሎም አቶ በቴ ኡርጌሳ ከህግ ውጪ በተፈጸመባቸው ግድያ ህይወታቸው ማለፉን ገልጾ ግድያው የኦሮሞን ጥያቄ ለማፈን እና አመራር አልባ ለማድረግ ነው ሲልም ገልጿል፡፡ በኦሮሞ ህዝብ የሚወደዱ ሰዎችን እያሳደዱ መግደል ቀጥሏል ያለው ኦነግ ድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ ተገድሎ እስካሁን ፍትህ አልተጠም ሲልም ፓርቲው አክሏል፡፡ አቶ በቴ ኡርጌሳ በተደጋጋሚ ጊዜ ለእስር ሲዳረጉ የቆዩ ሲሆን በቅርቡም " ሁከት እና ብጥብጥ በማስነሳት " ወንጀል ተጠርጥረዋል በሚል…
Read More
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ  አባል ለመሆን የመጨረሻው ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ  አባል ለመሆን የመጨረሻው ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ

ከ24 ዓመት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስር ለማሳለጥ የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥምረት በየጊዜው አዳዲስ አባላትን በመሳብ ላይ ይገኛል። ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ከአንድ ዓመት በፊት ይህን ጥምረት ለመቀላቀል በይፋ ከጠየቀች በኋላ ባሳለፍነው ሕዳር ወር ጀምሮ አባል መሆኗ ይታወሳል፡፡ ጥምረቱም የመቋዲሾን ጥያቄ ለመመለስ ባለሙያዎቹን አሰማርቶ የተለያዩ ግምገማዎችን ሲያደርግ ቆይቶ ሶማሊያን ስምንተኛዋ አባል ሀገር አድርጎ መቀበሉን በወቅቱ አስታውቋል። ዋና መቀመጫውን አሩሻ ታንዛኒያ ያደረገው ይህ የኢኮኖሚ ጥምረት በቀጣይ በሚያደርገው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያን በይፋ በአባልነት እንደሚቀበል ይጠበቃል። ዋና ጸሀፊው አክለውም “የጥምረቱ ቀጣይ አባል ሀገር ኢትዮጵያ ልትሆን ትችላለች፣ ኢትዮጵያ አባል የመሆን ፍላጎትም አሳይታለች” ሲሉ ተናግረውም ነበር፡፡ የህብረቱ ዋና ፀሐፊ የሆኑት ፔኒና ማንሎንዛ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በመከታተል እና ሪፖርቶችን በማውጣት የሚታወቀው ኔት ብሎክስ የ2023 ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ ተቋም ሪፖርት መሰረት ኢትዮጵያ ከኢንተርኔት በመዝጋት ገቢ ካጡ ሀገራት መካከል ከሩሲያ በመቀጠል ከፍተኛ ገቢ ያጣች ሀገር ተብላለች፡፡ ሩሲያ 113 ሚሊዮን ዜጎቿን ከኢንተርኔት ውጪ በማድረጓ አራት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ስታጣ ኢትዮጵያ ደግሞ 30 ሚሊዮን ገደማ ዜጎች ከኢንተርኔት አገልግሎት ውጪ ተደርገዋል፡፡ ሆን ተብሎ በመንግስት እንደተወሰደ የተገለጸው ይህ ኢንተርኔት ማቋረጥ ኢትዮጵያ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አሳጥቷታል ተብሏል፡፡ ሀገራት ኢንተርኔት አገልግሎቶችን የሚያቋርጡት በሶስት ምክንያት ነው የተባለ ሲሆን ተቃውሞዎችን ለማፈን፣ የሀሳብ ነጻነትን ለመገደብ እና የምርጫ ስራዎች እንዳይታወኩ በሚል እንደሆነም ተገልጿል፡፡ 25 የዓለማችን ሀገራት ኢንተርኔት አቋርጠዋል የተባለ ሲሆን…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መስጠት አቆመ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መስጠት አቆመ

በኢትዮጵያ ካሉ የንግድ ባንኮች መካከል አንጋፋ እና ሀብታም የሆነው የንግድ ባንክ ብድር መስጠቱን አቁሟል፡፡ ንግድ ባንኩ ብድር ለማግኘት የተለያዩ ሂደቶችን አልፈው ፤ ብድሩ ተፈቅዶላቸው የመልቀቅ ሂደት ላይ ያሉትም እንዲቆም ማዘዙ ተገልጿል፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የባንኩ ደንበኛ ለኢትዮ ነጋሪ እንዳሉት የንግድ ባንክ ብድር ተፈቅዶልኝ ገንዘቡን ለመረከብ በመጠባበቅ ላይ እያለሁ ብድሩ ለጊዜው እንዲቆም መወሰኑ ተነግሮኛል ብለዋል፡፡ ሌላኛው የባንኩ ደንበኛ በበኩሉ ሶስት ሚሊዮን ብር ብድር ለመውሰድ አስፈላጊውን መስፈርቶች ሁሉ አሟልቼ ብሩ እንዲለቀቅልኝ እየተጠባበቅሁ እያለ የቅርንጫፉ ስራ አስኪጅ ደውለው ብድሩ መታገዱን ነገሩኝ ሲልም ነግሮናል፡፡   ባንኩ ብድር እንዲቆም ትእዛዝ ያስተላለፈው ከመጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ነውም ተብሏል፡፡ ንግድ ባንኩ በጊዜያዊነት ብድር መልቀቅ…
Read More
ኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ከግብር ነጻ እድል ፈቀደች

ኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ከግብር ነጻ እድል ፈቀደች

የኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ለጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ወይም ስታርት አፕ የተለያዩ ማበረታቻዎችን መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ለስራ ፈጣሪዎች ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ከግብር ነጻ እድል፣ ከውጭ ንግዶች የሚያገኟቸውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ሙሉ ለሙሉ እንዲወስዱ፣ ንግድ ፈቃድ ለማውጣት የግድ ቢሮ ያስፈልግ የነበረውን ማንሳት፣ አዲ ሀሳብ ላላቸው ብድር ማመቻቸት እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ይህ አውደ ርዕይ ለ20 ቀናት ይቆያል የተባለ ሲሆን ጎብኚዎች ወደ ሳይንስ ሙዚየም በማቅናት መግባት እና መጎብኘት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡ ከተደረጉ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት…
Read More
ራስ ገዞቹ ሶማሊላንድ እና ፑንትላንድ ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ ተናገሩ

ራስ ገዞቹ ሶማሊላንድ እና ፑንትላንድ ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ ተናገሩ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከአራት ወራት በፊት በወደብ ጉዳይ በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት እንድትሆን ሶማሊላንድ ደግሞ የሀገርነት እውቅና እንድታገኝ የሚያደርግ በመሆኑ ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣንና እና ተቃውሞን አስከትሏል። ከትናንት በስቲያም ሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደርን በ72 ሰዓት ውስጥ ሞቃዲሾን ለቃ እንድትወጣ እና በሀርጌሳ እና ጋሮዌ ያሉ የኮንሱላ ጽህፈት ቤቶች እንዲዘጉ ሰራተኞቹም በሁለት ሳምንት ውስጥ ሶማሊያን ለቀው እንዲወጡ መወሰኗን አስታውቃለች፡፡ ራስ ገዟ ሶማላንድ እና ፑንት ላንድ የሶማሊያ መንግስት በሀርጌሳ እና ጋሮዌ የሚገኙ ቆንስላዎች እንዲዘጉ ያሳለፈውን ውሳኔ መቃወማቸው ተነግሯል። ይህንን ተከትሎም ሶማሊያ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

ኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ የ1 ነጥብ 72 ቢሊዮን ዶላር ወይም የ97 ቢሊዮን ብር እርዳታ እና በድር ስምምነት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ተወካይ የሆኑት ኦስማን ዲዮን ተፈራርመዋል ተብሏል፡፡ ከዓለም ባንክ ከተገኘው የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ 850 ሚሊዮን ዶላር ያህሉ በእርዳታ ለኢትዮጵያ የተለያዩ ስራዎችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ቀሪው ገንዘብ ደግሞ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት እና ለማከናወን በሚል በብድር መልኩ ከባንኩ እንደተሰጠ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ በእርዳታ ከተሰጠው ገንዘብ ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላሩ ለገጠር አካባቢዎች የምግብ ዋስትና፣ የአየር ንብረት ለውጥ ስራዎችን ለመደገፍ፣ 82 ዶላሩ ደግሞ በከተማ አካባቢዎች ምግብ ዋስትና ስራዎችን ለማረጋገጥ…
Read More
የኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ ዉይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ ዉይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት እና ሀገራት ጋር እያደረገችው ያለው ውይይት አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋሙ አይኤምኤፍ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይቶችን ከሚያደርጉ አበዳሪ ተቋማት መካከል ዋነኛው ሲሆን ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ቆይታ አድርጎ መመለሱ ተገልጿል፡፡ አይኤምኤፍ በድረገጹ ባወጣው መረጃ በኢትዮጵያ መንግስት ጥያቄ መሰረት ከመጋቢት 10 እስከ 24 ቀን 2016 ዓም ድረስ በአዲስ አበባ ቆይታ አድርጎ ተመልሷል፡፡ ኢትዮጵያ ልታካሂደው ባሰበችው የኢኮኖሚ ሪፎርም ላይ አይኤምኤፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥያቄ እንዳቀረበች የገለጸው ይሄው ተቋም በአልቫሮ ፒሪስ የተመራ የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ቡድን ወደ አዲ አበባ መምጣቱን አስታውቋል፡፡ ለ15 ቀናት በዘለቀው በዚህ የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ ባለሙያዎች እና ባለስልጣናት መካከል የተደረገው ውይይት ገንቢ እንደነበርም ተገልጿል፡፡…
Read More
መንግስት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን መቆጣጠር የሚያስችለውን ህግ አወጣ

መንግስት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን መቆጣጠር የሚያስችለውን ህግ አወጣ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን አጽድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ አጽድቋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ተስፋዬ በልጂጌ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ መንገግስት የዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት የሆነውን የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ለማሻሻል የተለያዩ ጥረቶች እያደረገ ቢሆንም፤ ከመኖሪያ ቤት ፍላጎት ጋር ሊጣጣም አልቻለም ብለዋል። አቶ ተስፋዬ አክለውም ፤ በኢትዮጵያ የተጋነኑ እና ከተከራዮች የመክፈል አቅም በላይ የሆነ የቤት ኪራይ ጭማሪዎች በከተሞች እንዳሉ ተናገረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ በተለይ በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ እና ዜጎችም ተረጋግተው ኑሯቸውን…
Read More
እየሰጡ መንሳት

እየሰጡ መንሳት

በበፍቃዱ ኃይሉ ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ከኃይለማርያም ደሳለኝ ከተረከቡ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ። ዐቢይ በእነዚህ ዓመታት የተከተሉት የአመራር ሥልት በፍቃዱ ኃይሉ “እየሰጡ መንሳት” የሚለው አባባል ይገልጸዋል የሚል አተያይ አለው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን የሥልጣን ማማ ከተቆናጠጡ እነሆ ዛሬ መጋቢት 24፣ 2016 ስድስት ዓመት ሞላቸው። በዘመናዊ ፖለቲካ ከአንድ የአገር መሪ የሚጠበቁት መሠረታዊ ኃላፊነቶች ሰላም እና መረጋጋት ማስፈን፣ ሕግ እና ስርዓት ማበጀት እንዲሁም ሥራ መፍጠር እና ኢኮኖሚ ማረጋጋት ናቸው። እነዚህ ዘርፎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እምብዛም ናቸው። ይልቁንም በነውጥ እና ወጀብ እየተላጋች በምትሔደው መርከብ ውስጥ ወደ ካፒቴኑ መንበር ለመውጣት እርካቡ ላይ መንጠላጠል እንዲሁም መንበሩ ላይ ተደላድሎ መቀመጥ ግን ይችሉበታል። ይህንን…
Read More