01
Mar
በአማራ ክልል መዲና ባህርዳር ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከባድ ተኩስ ሲካሄድ እንደነበር ነዋሪዎች ነግረውናል፡፡ ለደህንነታቸው የሰጉ እና ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የባህርዳር ከተማ ነዋሪ እንዳሉን ከሆነ ከዛሬ ማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ የተኩስ ድምጽ መስማታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ነዋሪው አክለውም በፍርሃት ቤት ውስጥ በራቸውን ዘግተው ቤተሰባቸውን ይዘው መቀመጣቸውን የነገሩን እኝህ ነዋሪ በተለይም እስከ ጠዋቱ 3 ሰዓት ድረስ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ መካሄዱንም ነግረውናል፡፡ ውጊው በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል መካሄዱን እርግጠኛ ነኝ የሚሉን እኝህ ነዋሪ ንጹሃን ከቤታቸው ባለሙውጣታቸው የከፋ ጉዳት እንዳላስተናገዱም አክለዋል፡፡ አሁን ላይ በተለይም ከምሳ ሰዓት ጀምሮ የውጊያ ድምጽ እየሰሙ እንዳልሆነ አንቡላንሶች በመንገዶች ላይ ሲመላለሱ መመልከታቸውንም ነግረውናል፡፡ ሌላኛው በባህር ዳር መሀል ከተማ…