Amhara

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው መታሰሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው መታሰሩ ተገለጸ

በበርካታ የኢትዮጵያ ብዙሃን መገናኛ ተቋማት በጋዜጠኝነት ሙያ ያገለገለው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በጽጥታ ሀይሎች መታሰሩን የስራ ባልደረቦቹ ለኢትዮ ነጋሪ ተናግረዋል ። ጋዜጠኛ ዳዊት ከሌሎች የስራ ባልደረቦቹ ጋር በመሆን አራት ኪሎ ሚዲያ የተሰኘ የድጅታል ሚዲያ አቋቁሞ በመስራት ላይ ይገኝ ነበር። ጋዜጠኛው ለስራ ወደ ባህርዳር ከተማ ባቀናበት ወቅት ዛሬ ሚያዝያ 4 ቀን 2015 ዓ.ም በጸጥታ ሀይሎች ተይዞ መወሰዱን ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የሙያ ባልደረቦቹ ነግረውናል። ይሁንና የአማራ ክልልም ይሁን የፌደራል መንግሥት በጋዜጠኛ ዳዊት እስር ጉዳይ እስካሁን ያሉት ነገር የለም። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ህዝብ ግንኙነት ኮለኔል ጌትነት ስለ ጋዜጠኛው እስር እንደማያውቁ ተናግረዋል። ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት፣ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ ኢትዮ…
Read More
መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን ጉዳይ በውይይት እንዲፈታ ኢሰመኮ አሳሰበ

መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን ጉዳይ በውይይት እንዲፈታ ኢሰመኮ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰሞኑ የክልል ልዩ ሀይሎችን በሚመለከት በተፈጠሩ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል። ተቋሙ እንዳለው የልዩ ሀይሎችን መልሶ የማደራጀትን ውሳኔ ትግበራ በውይይትና የሰዎችን ሰብአዊ መብቶች አደጋ ላይ በማይጥል ሁኔታ ሊከውን ይገባል ሲል አሳስቧል ኢሰመኮ መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን በፌዴራልና በክልል መደበኛ የጸጥታ ኃይሎች ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ መልሶ ለማደራጀት ያሳለፈውን ውሳኔና ትግበራ መጀመሩን ተከትሎ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ ተቃውሞዎች፣ የጸጥታ መደፍረስ እና በአንዳንድ አካባቢዎች የደረሱ ግጭቶችንና ጉዳቶችን በተመለከተ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጿል። ኮሚሽኑ በተለይም በቆቦ፣ በባሕር ዳር፣ በወረታ፣ በኮምቦልቻ፣ በደብረ ብርሃን እና በመራዊ የተቃውሞ ሰልፎች፣ መንገድ መዘጋት፣ የአገልግሎት መቋረጥ እንዲሁም በጸጥታ ኃይሎች መካከል ፍጥጫዎች የተከሰቱ ሲሆን፤ በአንዳንድ አካባቢዎች…
Read More
በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

የደብረብርሃን ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሪት መሰረት መንገሻ እንደገለጹት ከትላንት ጀምሮ መርዝ ተጨምሮበት ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ተቋማቸው አንዱ ተግባሩ የሚያመርተውን ውሃ ጥራት አረጋግጦ ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት ሃላፊነታቸው በመሆኑን ባለሙያዎች እሁድ ቅዳሜን እና የበዓላትን ቀናት ጭምር አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋኖች ታጥረው የሚጠበቁ ከመሆኑም በላይ ሁል ጊዜ በባለሙያ ክትትል እየተደረገላቸው ውሃው በባለሙያ ጥራቱ ተረጋግጦ ለደንበኞች እንደሚሰራጭ አረጋግጠዋል፡፡ የፀጥታ ችግር ሲከሰት ደግሞ በልዩ ሁኔታ ጥበቃና ክትትል እንደሚደረግላቸው ጠቁመዋል፡፡ ችግር ካጋጠመም ውሃው እንደማይለቀቅ ጠቅሰው ህብረተሰቡ የውሃ ተቋሙ የሚያደርገውን ጥንቃቄ በአግባቡ ተረድቶ በአሉባልታ ወሬ እንዳይረበሽ መክረዋል፡ ውሃው 100 ፐርሰንት ንጹህ መሆኑን ስራ አስኪያጇ መልዕክታቸውን…
Read More
በደብረ ብርሃን መከላከያ ሰራዊት ወደ ከተማዋ እንዳይገባ በሚል የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተገለጸ

በደብረ ብርሃን መከላከያ ሰራዊት ወደ ከተማዋ እንዳይገባ በሚል የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተገለጸ

ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ በሚያስኬደው ዋና መንገድ ደብረ ብርሃን ከተማ አቅራቢያ በመከላከያ እና የመንግሥትን ውሳኔ ባልተቀበሉ ኃይሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ ይገኛል። የተኩስ ልውውጡ የተጀመረው "መከላከያ ያልፋል አያልፍም" በሚል አለመግባባት መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢትዮ ነጋሪ ተናግረዋል። ተኩሱ ከተጀመረ አንድ ሰዓት ያለፈው ሲሆን፤ የተኩስ ልውውጡ ዳሸን ቢራ ፋብሪካ አካባቢ የሚገኙ የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና "ፋኖ" በመባል የሚታወቀው ታጣቂ ኃይል እና በመከላከያ መካከል እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የከተማዋ እና የአካባቢው ነዋሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአማራ ልዩ ሀይሎችን ትጥቅ ያስፈታል በሚል አዳራቸውን ሲጠብቁ እንዳደሩ እና ዛሬ ረፋድ ጀምሮ ግን የተኩስ ልውውጡ መጀመሩን ከነዋሪዎች ሰምተናል፡፡ በከተማዋ የመንግስትን እቅድ ተቃውሞ መጀመሩን ተከትሎ ትናንት እና ዛሬ የግል…
Read More
በአጣዬ ዙሪያ ዳግም ጦርነት ተነሳ

በአጣዬ ዙሪያ ዳግም ጦርነት ተነሳ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ኦሮሚያ ብሄረሰብ ዞኖች አዋሳኝ አካባቢዎች ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ጦርነት መጀመሩን የአይን እማኞች ለኢትዮ ነጋሪ ገልጸዋል፡፡ በኦሮሞ በሄረሰብ ዞን ስር ካሉ ወረዳዎች መካከል አንዱ ከሆነው ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ሰንበቴ ከተማ የተነሱ ታጣቂዎች ወደ ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ ስራ ካለችው አላላ ቀበሌ በመሄድ የሰብል ስብሰባ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮች ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ነዋሪዎቹ አክለዋል፡፡ ተኩሱን ተከትሎም ወደ አካባቢው ባሉ ሌሎች ቀበሌዎች ጦርነት የተጀመረ ሲሆን ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸውን ጥለው ተሰደዋል ተብሏል፡፡ በአካባቢው የነበረው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጦርነቱን ለማስቆም ሞክሮ እንዳልተሳ የነገሩን ነዋሪዎቹ ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ተጨማሪ ሀይል ከአጎራባች አካባቢዎች በመግባት ላይ ነውም ብለውናል፡፡ ከሁለት ወር በፊት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ…
Read More
በአማራ ክልል ለሶስተኛ ቀን ተቃውሞ ቀጥሏል

በአማራ ክልል ለሶስተኛ ቀን ተቃውሞ ቀጥሏል

በአማራ ክልል ለሶስተኛ ቀን ተቃውሞ ቀጥሏል የፌደራል መንግሥት የተማከለ የጸጥታ ሀይል ለመመስረት ማቀዱን ተከትሎ የክልል ልዩ ሀይሎች እንዲፈርሱ ውሳኔ አስተላልፏል። ህጋዊ መሰረት የለውም የሚባለው የክልል ልዩ ሀይል አባላት ወደ ፌደራል ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ እና መደበኛ ፖሊስ እንዲደራጁም ትግበራ መጀመሩን የፌደራል መንግሥት አስታውቋል። ይሁንና በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የመንግሥትን ውሳኔ የተጠራጠሩ እና የተቃወሙ ሰዎች ወደ አደባባይ ለተቃውሞ ወጥተዋል። በተለይም በሰሜን ወሎ፣ ጎጃም እና ሌሎችም አካባቢዎች መንገዶች በተቃዋሚዎች የተዘጉ ሲሆን ወደ ዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶችም ተዘግተዋል። ይህን ተከትሎም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል የሚያስኬዱ መንገዶች በከፊል ተዘግተዋል። ህዝቡ ወደ አደባባይ የወጣው የትግራይ…
Read More
በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

በአማራ ክልል ልዩ ኃይልን እና በፌደራል የጸጥታ ኃይሎች መካከል ውጥረት መፈጠሩ ተገለጸ

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን በግዴታ ትጥቅ ለማስፈታት እንቅስቃሴ በመጀመሩ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፤ በክልሉ ልዩ ኃይል እና በፌዴራል የጸጥታ ተቋማት መካከል ከፍተኛ ውጥረት መፈጠሩን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አስታወቀ፡፡ የክልሉን ልዩ ኃይል ያለ በቂ ዝግጅት፣ ውይይት፣ የጋራ መግባባትና መተማመን ሳይደረስ በድንገት እና ያለበቂ የጸጥታ ዋስትና ለማፍረስ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ እና ውሳኔውን ለማስፈጸም እየሄደበት ያለው መንገድ ኃላፊነት የጎደለው መሆኑን አብን አስታውቋል፡፡ ጉዳዩ በአማራ ክልል ብቻ ሳይወሰን በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አለመረጋጋት የሚፈጥር፣ ክልሉን እና  ኢትዮጵያን ወደ ሌላ የቀውስ አዙሪት የሚከት አደገኛ አካሄድ መሆኑን አብን ለፌዴራሉ መንግሥትና ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አሳስቧል፡፡ በመሆኑም፣ የገዥው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ውሳኔውን በአፋጣኝ እንዲቀለብስ እና ከአማራ…
Read More
በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚቃወም እና የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚቃወም እና የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

በኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን የመጡበትን ቀን በድጋፍ ሰልፍ ሲያከብሩ በአማራ ክልል ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን የመጡባትን ቀን መከራ እና ሞት እንጂ ለውጥ አላመጣልንም ሲሉ በሰላማዊ ሰልፍ ላይ ገልጸዋል፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት በህወሃት የበላይነት ይመራ የነበረው ኢህአዴግ ህዝባዊ ተቃውሞ መበርታቱን ተከትሎ ነበር የወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ሀይለማርያም ደሳለኝ መጋቢት 2010 ዓ.ም ስልጣን የለቀቁት፡፡ ይህን ተከትሎም አብይ አህመድ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን ተክተው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም ሹመቱን በተቀበሉበት ወቅት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ የበርካቶችን ድጋፍ እና አድናቆት ያገኙ ቢሆንም በሁለት ዓመት ውስጥ ግን ድጋፋቸው አሽቆልቁሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለይም…
Read More
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የህወሀትን ከሽብር መዝገብ መሰረዝን ተቃወሙ

የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባት (ህወሀት) በትግራይ ክልል ያለውን የሀገር መከላከያ ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተጀመረው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት ከ800 ሺህ በላይ ዜጎችን እና ከ20 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ የንብረት ውድመት አድርሷል። በፌደራል መንግሥት እና ህወሀት መካከል የተደረገው ይህ ጦርነት ባሳለፍነው ህዳር በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። ይህን ስምምነት ተከትሎም ጦርነቱ የቆመ ሲሆን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት በመመስረት ላይ ይገኛል። እንዲሁም ህወሀት በግንቦት 2021 ላይ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ ነበር። ይህ ህግ አውጪ ምክር ቤት ባሳለፍነው ሳምንት ህወሀትን ከሽብር መዝገብ ላይ ሰርዟል። የኢትዮጵያ ማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ እና የአማራ…
Read More
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በሚመለከት በአሜሪካ የወጣውን መግለጫ ውድቅ አደረገችየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ሁሉም ተሳታፊዎች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን አስታውቋል። ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል ሲል የደረሰችበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።  በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።  የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ…
Read More