ስፖርት

ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ጦርነት እና እግር ኳስ በኢትዮጵያ….

ቢኒያም ተክለወይኒ እባላለሁ። ትውልዴ ሽረ ነው። ከጦርነቱ በፊት የፕሪሚየር ሊጉ ተካፋይ የሆነው የስሑል ሽረ ዋና ቡድን ተጨዋች ነበርኩ ። ሊብሮ ነኝ ። አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ዋና አሰልጣኛችን ነበር ። ኳስ እወዳለሁ ። ደጉ ደበበን አደንቃለሁ ። እንደ እርሱ የመሆን ምኞት ነበረኝ ። ተቀራኒ ሆነን ተጫውተናልም:: በኳስ ጨዋታ መከላከልን እወዳለሁ ። አዳነ ሳላ አማኑኤልን ጨምሮ ከብዙ ጎበዝ አጥቂዎች ተፋጥጫለሁ ። ሁሉንም ገትሬ አቁሜያለሁ ። ቡድኔ ጎል እንዳይቆጠርበት በአግባቡ መምራት መከላከል ከስሑል ሽረ ጋር በፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን መሆን የዘወትር ህልሜ ነበር ። ከሽረ ውጭ ሌላ ክለብ አላውቅም ። በኳስ ጨዋታ መንገዴ የእራሴንም የቤተሰቦቼንም ህይወት መቀየር ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተመርጦ መጫወት የሌት ተቀን…
Read More
ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

ወደ አሜሪካ ካቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ ሁለት ሰዎች መጥፋታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቅርቡ ወደ አሜሪካ አቅንቶ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን አድርጎ ተመልሷል። ፌዴሬሽኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአሜሪካ ቆይታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ብሔራዊ ቡድኑ በአሜሪካ ቆይታው አላማውን እንዳሳካ የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን በመግለጫው ላይ ተናግረዋል። የዲሲ ዩናይትድ ድርሻ ያላቸው አቶ እዮብ ማሞ ከፌዴሬሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ በቅርቡ ከስምምነት እንደሚደርሱም አቶ ባህሩ ገልጸዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በቅርቡ ወደ አሜሪካ በማቅናት ስምምነቱን ይፈፅማሉም ብለዋል። ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚደረገው ስምምነት ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾች በዲሲ ዩናይትድ የመጫወት እድልን እንዲያገኙ እንደሚያስችል አቶ ባህሩ አክለዋል። ይሁንና የቡድኑ የትጥቅ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አውግቼ እና የፊዚዮቴራፒ ባለሙያው…
Read More
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድር መርሀ ግብር ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድር መርሀ ግብር ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 የውድድር ዓመት የጨዋታ እጣ ድልድልበአዲስ አበባ ይፋ ሆኗል። በዚህ መሰረት ሀምበርቾ ዱራሜ ከድሬዳዋ ከተማ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታውን የሚያደርጉ ሲሆን ሻሸመኔ ከተማ ከወላይታ ዲቻ፣ ሀዋሳ ከተማ ከፋሲል ከተማ የፊታችን መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ. ም ያደርጋሉ። እንዲሁም አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ኢትዮጵያ መድህን ከከባህርዳር፣ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ ቡና፣ ሀዲያ ሆሳዕና ከመቻ የፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎችን ይጫወታሉም ተብሏል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ካምፓኒ ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ በዕጣ አወጣጥ ስነ ስርዓቱ ላይ እንዳሉት ለተወዳዳሪ ክለቦች መልካም የውድድር ዓመት እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል። በ2015 የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ስያሜ መብትን ቤትኪንግ ይዞ እንደነበር የገለጹት ስራ አስኪያጁ የ2016 የሊግ…
Read More
ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ

ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ

ጣልያናዊው ጂያንሉጂ ቡፎን ጓንቱን ሰቀለ የጣልያን ብሔራዊ ቡድን እና ጁቬንቱስ ታሪካዊ ግብ ጠባቂ ጂያንሉጂ ቡፎን በ 45 ዓመቱ ከውድድር ራሱን እንዳገለለ አስታውቋል። ጂያንሉጂ ቡፎን በጣልያኑ ክለብ ጁቬንቱስ ቤት አስራ ሰባት አመታትን ያሳለፈ ሲሆን በክለቡ 685 ጨዋታዎች በማድረግ በክለቡ ታሪክ ብዙ ጨዋታ ያደረገ ሁለተኛው ተጨዋች ነው። ሀያ ስምንት አመታትን በተጨዋችነት ያሳለፈው የ45 ዓመቱ ጂያንሉጂ ቡፎን ከጣልያን ብሔራዊ ቡድን ጋር በ2006 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። ለጣልያን ብሔራዊ ቡድን 176 ጨዋታዎችን ያደረገው ቡፎን ለብሔራዊ ቡድኑ ብዙ ጨዋታዎችን በማድረግ ታሪካዊ ተጫዋች ነው። ተጫዋቹ ከጁቬንቱስ በተጨማሪ ወደ ፓሪስ በማቅናት በፒኤስጂ እግር ኳስ ክለብ ውስጥ ለአንድ ዓመት በግብ ጠባቂነት አገልግሏል።
Read More
ኢትዮጵያ ለአደይ አበባ ስታድየም አዲስ የግንባታ ጨረታ ልታወጣ ነው

ኢትዮጵያ ለአደይ አበባ ስታድየም አዲስ የግንባታ ጨረታ ልታወጣ ነው

ለረዥም ጊዜ ተቋርጦ የቆየውን የአደይ አበባ ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ በአዲሱ በጀት ዓመት እንደገና ለማስጀመር በጀት መያዙን ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ገልጿል ። የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በ48 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባውና 62ሺ ተመልካች የመያዝ አቅም ያለው ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታን ለማስቀጠል በ2016 ዓ.ም በጀት የተያዘለት በመሆኑ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቶ ግንባታው ይጀመራል። የብሔራዊ ስታዲየሙ ግንባታ በቻይናው ኩባንያ ይካሄድ እንደነበረ አስታውሰው፤ ግንባታው በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱን ገልፀዋል። በኋላም የግንባታ ተቋራጩ ለሥራው ያቀረበው የዋጋ ማስተካከያ ከገበያ በላይ የተጋነነ በመሆኑ መንግሥት ከያዘው በጀት ጋር ሊመጣጠን አልቻለም። በዚህም ከግንባታ ተቋራጩ ጋር ያለው ውል እንዲቋረጥ መደረጉን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።…
Read More
ሳላሀዲን ሰኢድ ጫማውን ሰቀለ

ሳላሀዲን ሰኢድ ጫማውን ሰቀለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከፍተኛ ግብ አግቢ ሳላሀዲን ሰዒድ ኳስ መጫወት ማቆሙን ገልጿል በአሶሳ ተወልዶ ያደገው ሳላሀዲን ለበርካታ የውጪ እና የሀገር ውስጥ ክለቦች መጫወት ችሏል ሳላሀዲን ሰኢድ ጫማውን ሰቀለ። በተለያዩ ክለቦች እና በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለበርካታ አመታት በመጫወት የሚታወቀው ገልግሎት ሳላዲን ሰዒድ ጫማውን ሰቅሏል፡፡ ላለፉት 15 ዓመታት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ አይረሴ ታሪኮችን ያስመዘገበው ሳላዲን እግር ኳስ መጫወቱን እንዳቆመ ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል። ተጫዋቹ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባለፈ ለሙገር ሲሚንቶ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ለሲዳማ ቡና እንዲሁም ከውጪ ደግሞ ለግብጾቹ ዋዲዳግላ እና አልአህሊ፣ ለአልጀሪያው መውሊዲያ አሊደር እና ለቤልጂየሙ ሊርስ እግር ኳስ ክለቦች መጫወት ችሏል። በ37 ዓመቱ ራሱን ከእግር ኳስ ጨዋታ ያገለለው ሳላዲን በተያዘው ዓመት…
Read More
ናይጄሪያ አውስትራሊያን በማሸነፍ በዓለም ዋንጫው ቆይታዋን አለመለመች

ናይጄሪያ አውስትራሊያን በማሸነፍ በዓለም ዋንጫው ቆይታዋን አለመለመች

ናይጄሪያ አውስትራሊያን በማሸነፍ በዓለም ዋንጫ ውድድር ያላትን ቆይታ አለምልማለች። በአውስትራሊያ እና ኒውዝላንድ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ያለው የፊፋ ሴቶች ዓለም ዋንጫ ከተጀመረ ስምንተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል። አፍሪካ በዚህ ውድድር በናይጀሪያ፣ ዛምቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ተወክላለች። ናይጀሪያ በዛሬው ዕለት ከአውስትራሊያ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ ከመመራት ተነስታ 3ለ2 ማሸነፍ ችላለች። ናይጀሪያ ማሸነፏን ተከትሎ ምድቧን በአራት ነጥብ መምራት የጀመረች ሲሆን ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ አንድ ነጥብ ብቻ በቂዋ ይሆናል። አፍሪካን በዚህ ውድድር የወከሉት ሌሎቹ ብሔራዊ ቡድኖች ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ እድላቸው የመነመነ ሲሆን ሞሮኮ አስቀድማ ከውድድሩ ተሰናብታለች። የሴቶች ዓለም ዋንጫ ውድድር እስከ ነሀሴ 20 ቀን 2023 ውስጥ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ይካሄዳል። ከዚህ በፊት የሴቶች…
Read More
የሴቶች ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል

የሴቶች ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል

እንደ ወንዶች የዓለም ዋንጫ ሁሉ በየ አራት አመቱ የሚካሄደው የሴቶች እግር ኳስ ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል። አውስትራሊያ እና ኒውዝላንድ በጋራ የሚያስተናገዱት የ2023 የፊፋ ሴቶች ዓለም ዋንጫ አዘጋጆቹ አውስትራልያ እና ኒውዝላንድ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታን ያደርጋሉ። ውድድሩ ከፈረንጆቹ ሀምሌ 20 እስከ ነሀሴ 20 ቀን 2023 ውስጥ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ይካሄዳል ተብሏብ። ከዚህ በፊት የሴቶች ዓለም ዋንጫ በ24 ብሔራዊ ቡድኖች አማካኝነት ይካሄድ የነበረ ሲሆን በዘንድሮው ግን ፊፋ የተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 32 ከፍ አድርጎታል። አፍሪካ በዚህ ውድድር ላይ በአራት ሀገራት የሚወከሉ ሲሆን ናይጀሪያ ፣ ዛምቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ተሳታፊ ሀገራት ናቸው። የናይጀሪያዋ አሲሳት ኦሾላ በውድድሩ ትደምቃለች ተብሎ ከወዲሁ ትኩረት የተሰጣት ተጫዋች…
Read More
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ቀዳሚ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ቀዳሚ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

የአልናስር አጥቂ የሆነው ፖርቹጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልድ የ2023 ከፍተኛ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆኖ ተመዝግቧል። እንደ ፎርብስ ዘገባ ከሆነ የአምስት ጊዜ ባሎንዶር ተሸላሚው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በተያዘው ዓመት ብቻ 136 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የዓለም ዋንጫ አሸናፊው አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ በ2022 ዓመት 130 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ተከፍሎታል። ክርስቲያኖ ካገኘው የ136 ሚሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ውስጥ 90 ሚሊዮን ዶላሩን ከሜዳ ውጪ ማለትም ከማስታወቂያ እና ስፖንሰር ስራዎች ማግኘቱ ተገልጿል። በማንችስተር ዩናይትድን ባለ መግባባት ወደ ሳውዲ አረቢያው አልናስር ያመራው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ደመወዙ እጥፍ እንዳደገለትም ተገልጿል። በአጠቃላይ በስፖርቱ ዘርፍ ሊዮኔል ሜሲ እና ክሊያን ምባፔ ከክርስቲያኖ ሮናልዶ በመቀጠል ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዱረጃን ይዘዋል። የቅርጫት ኳስ ኮኮቡ ለቦርን 119 ሚሊዮን…
Read More
ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የዘንድሮውን የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አንስቷል። ባህርዳር ከነማ ውድድሩን በሁለተኝነት አጠናቋል። የ2015 የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ አሸናፊነት ተጠናቋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ64 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ባህርዳር ከነማ ደግሞ በ60 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን በ49 ነጥቦች የውድድር ዓመቱን አጠናቀዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ወይም ፈረሰኞቹ ፕሪምየር ሊጉን ለ31ኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነዋል። የወራጅነት ደረጃዎች ላይ ደግሞ አርባምንጭ እግር ኳስ ክለብ በ34 ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ ክለብ በ18 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ15 ነጥቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርደዋል። የኮኮብ ግብ አግቢነት ደረጃውን የቅዱስ ጊዮርጊሱ እስማኤል አጎሮ በ25 የውድድር ዓመቱ ኮኮብ ግብ አግቢ ሆኖ አጠናቋል።
Read More