FIFA

የሴቶች ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል

የሴቶች ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል

እንደ ወንዶች የዓለም ዋንጫ ሁሉ በየ አራት አመቱ የሚካሄደው የሴቶች እግር ኳስ ዓለም ዋንጫ ነገ ይጀመራል። አውስትራሊያ እና ኒውዝላንድ በጋራ የሚያስተናገዱት የ2023 የፊፋ ሴቶች ዓለም ዋንጫ አዘጋጆቹ አውስትራልያ እና ኒውዝላንድ የመክፈቻ ውድድር ጨዋታን ያደርጋሉ። ውድድሩ ከፈረንጆቹ ሀምሌ 20 እስከ ነሀሴ 20 ቀን 2023 ውስጥ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ ይካሄዳል ተብሏብ። ከዚህ በፊት የሴቶች ዓለም ዋንጫ በ24 ብሔራዊ ቡድኖች አማካኝነት ይካሄድ የነበረ ሲሆን በዘንድሮው ግን ፊፋ የተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 32 ከፍ አድርጎታል። አፍሪካ በዚህ ውድድር ላይ በአራት ሀገራት የሚወከሉ ሲሆን ናይጀሪያ ፣ ዛምቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ተሳታፊ ሀገራት ናቸው። የናይጀሪያዋ አሲሳት ኦሾላ በውድድሩ ትደምቃለች ተብሎ ከወዲሁ ትኩረት የተሰጣት ተጫዋች…
Read More