ስፖርት

የቻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ሆነ

የቻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ሆነ

ሀያላን የአውሮፓ እግር ኳስ ክለቦች የሚፋለሙበት ተወዳጁ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ቀጣይ ጨዋታዎች ድልድል ተካሂዷል፡፡ የዓምናው የቻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው የእንግሊዙ ማንችስተር ሲቲ ከዴንማርኩ ኮፐንሀገን ጋር ተደልድሏል፡፡ እንዲሁም ምድቡን በበላይነት ያጠኛቀቀው አርሰናል ከፖርቹጋሉ ፖርቶ ጋር ሲደለደል ናፖሊ ከባርሴሎና፣ ፒኤስጂ ከሪያል ሶሴዳድ፣ የአምናው የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተር ሚላን ከአትሌቲኮ ማድሪድ፣ ፒኤስቪ ከቦሩሲያ ዶርትሙንድ፣ ላዚዮ ከባየር ሙኒክ እንዲሁም ላይፕዝሽ ከሪያል ማድሪድ እንደሚጫወቱ ተገልጿል፡፡ ናፖሊ ከባርሴሎና፣ ላይፕዝሽ ከሪያል ማድሪድ እና ኢንተር ሚላን ከአትሌቲኮ ማድሪድ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ከባድ ፉክክር ሊደረግባቸው የሚችሉ ጨዋታዎች እንደሚሆኑ ተጠብቋል፡፡ አራት የስፔን ክለቦች ወደ 16 ውስጥ በመግባት የቻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ያለፉ ሲሆን ጣልያን ሶስት እንግሊዝ እና ጀርመን ሁለት ሁለት ክለቦቻቸው ይሳተፋሉ፡፡ የ2022/23…
Read More
የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

በስፔኗ ቫሌንሲያ የተካሄደው የማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ የሚነግሱባት የስፔኗ ቫሌንሲያ ዛሬም ኢትዮጵያዊያን ተመሳሳይ ድሎችን አግኝተውባታል፡፡ በዚው ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአንደኝነት አጠናቀዋል፡፡ በሴቶች የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን ከአንደኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በበላይነት ሲያሸንፉ አትሌት ውርቅነሸ ደገፈ፣ አልማዝ አያና እና ህይወት ገብረኪዳን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ጠናቀዋል፡፡ በዚህ የወንዶች የማራቶን ውድድር ላይ አትሌት ሲሳይ ለማ አንደኛ፣ ኬንያዊው አትሌት አሌክሳንደር ሙቲሶ ሁለተኛ እንዲሁም ዳዊት ወልዴ እና ቀነኒሳ በቀለ ሶተኛ እና አራተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ አትሌት ሲሳይ ለማ ርቀቱን 2:01:48 በሆነ ሰአት ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ሲችል ተጠብቆ የነበረው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቡርኪናፋሶ አቻው 3 ለ 0 ተሸነፈ

ዋልያዎቹ በዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ጨዋታ በቡርኪና ፋሶ አቻቸው 3 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡ የቡርኪናፋሶን የማሸነፊያ ግቦች ብላቲ ቱሬ በ69 ኛው፣ በርትራንድ ትራኦሬ በ78ኛው እንዲሁም ዳንጎ ኦታትራ 90ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም በ2026 ካናዳ ሜክሲኮ እና አሜሪካ በጥምረት ለሚያዘጋጁት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አንድ የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድቡ 1 ነጥብ በመያዝ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ የአለም ዋንጫ የምድቡን ሶስተኛ እና አራተኛ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከጊኒ ቢሳኦ እና ጅቡቲ ጋር የሚያደርግ ይሆናል፡፡
Read More
የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

አትሌት ትግስት አሰፋ ለአለም አትሌቲክስ በዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ ምርጥ 10 የዓለም አትሌቶች መካከል አንዷነበረች። የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ2023 ዓመት በተካሄዱ የተለያዩ ውድድሮች ላይ ስኬታማ የሆኑ አትሌቶችን ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በመጀመሪያው ዙር 11 ምርጥ የዓለማችን አትሌቶች ዝረዝር ውስጥም የ5 ሺህ ሜትር ባለ ሪከርዷ ጉዳፍ ጸጋዬ እና የማራቶን ባለሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ አትሌቶች ነበሩ። ዎርልድ አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በውድድሩ ለመጨረሻ ዙር ያለፉ አትሌቶችን ዝርዝር አውጥቷል። በዚህም የማራቶን ባለሪከርዷ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለመጨረሻ ዙር ውድድር ከቀረቡ አትሌቶች መካከል እንዷ ሆናለች። ከአትሌት ትግስት አሰፋ በተጨማሪ ኬንያዊቷ አትሌት ፋይዝ ኪፕዬጎን፣ ጃማይካዊቷ ሸሪካ ጃክሰን፣ የኔዘርላንዷ…
Read More
አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ዋልያዎቹን በአሰልጣኝነት ተረከቡ

አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ዋልያዎቹን በአሰልጣኝነት ተረከቡ

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሐየራዊ ቡድን አሰልጣን የነበሩት ገብረመድህን ሀይሌ በድጋሚ ዋልያዎቹን እንዲያሰለጥኑ ተመርጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ መድን እግር ኳ ክለብን በማሰልጠን ላይ የነበሩት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ በአንድ ዓመት ውል ብሔራዊ ቡድኑን እንዲያሰለጥኑ ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኙ የብሔራዊ ቡድን ስራቸውን ከኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ ጋር ደርበው እንዲያካሂዱ ከፌዴሬሽኑ ጋር እንደተስማሙም ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ የሚያደርጋቸውን ሁለት ቀጣይ የሜዳው ጨዋታዎችን ወደ ሞሮኮ ተጉዘው ያካሂዳሉም ተብሏል። የመጀመርያው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ከሴራሊዮን ኅዳር 5 እንዲሁም ሁለተኛው ጨዋታ ከቡርኪና ፋሶ ጋር ኅዳር 11 የሚደረግ ሲሆን ሁለቱም ጨዋታዎች በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ይደረጋሉ፡፡ ብሄራዊ ቡድኑን በኢንተርናሽናል ውድድር ተፎካካሪ ማድረግ የሚጠብቅባቸው አሰልጣኝ ገብረመድህን…
Read More
ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል አደረጉ

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል አደረጉ

የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ በላቲቪያ ሪያ በመደረግ ላይ ሲሆን የወንዶች እና የሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ፍጻሜውን አግኝቷል። በወንዶች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት ውድድሩን አጠናቀዋል። አትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት 12:59 በሆነ ሰዓት ውድድሩን በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ደግሞ በ13:02 በመግባት ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል። ኢትዮጵያዊው አትሌት ሀጎስ ገብረ ህይወት የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ የወንዶች 5ኪ.ሜ ውድድርን ማሸነፍ የቻለ የመጀመሪያው አትሌት ሆኗል። በሴቶች ተመሳሳይ ርቀት ውድድር ኬንያዊያኑ አትሌት ቺቤት አንደኛ እንዲሁም ናሬንጉሩክ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች እጅጋየሁ ታዬ እና መዲና ኢሳ ደግሞ ሶስተኛ እና አራተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። በሌላ የ1 ማይል ርቀት ውድድር ደግሞ አትሌት ድርቤ ወልተጂ ኬንያዊቷን የ 1500ሜ…
Read More
ስድስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአበረታች መድሀኒት ምክንያት ለዓመታት ከውድድሮች ታገዱ

ስድስት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአበረታች መድሀኒት ምክንያት ለዓመታት ከውድድሮች ታገዱ

የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በተጠረጠሩ አትሌቶች ላይ ጊዜያዊ እገዳ በመጣል ጉዳዩን ሲያጣራ መቆየቱን አስታውቋል። እገዳ የተላለፈባቸው አይሌቶች አትሌት ሹሜ  ጣፋ ደስታ እና  አትሌት መንግስቱ በቀለ ተዴቻ  የተከለከሉ አበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግ በመጠቀም የህግ ጥሰት የፈፀሙ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብላል። በዚህም መሠረት የረጅም ርቀት ሯጭ የሆነዉ አትሌት  ሹሜ ጣፋ ደስታ 5-methylhexan-2-amine የተባለውን የተከለከለ ንጥረ-ነገር ተጠቅሞ በፈፀመው  የፀረ-አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት በውድድሩ ያስመዘገበው ውጤት እንዲሰረዝ እና  እ.ኤ.አ ከግንቦት 25/2023  ጀምሮ ለአራት (4) አመታት በማንኛውም ስፖርታዊ ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ  የቅጣት ውሳኔ እንደተላለፈበት ተገልጿል። በተመሳሳይ መልኩ አትሌት መንግስቱ በቀለ ተዴቻ ቻይና አገር ውስጥ በነበረው ውድድር ላይ Erythropoietin (EPO) የተባለዉን የተከለከለ አበረታች ቅመም ተጠቅሞ በመገኘቱ የፀረ-…
Read More
ኢትዮጵያ በቡዳፔስት ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ ስድስተኛ ሆና አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በቡዳፔስት ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ላይ ስድስተኛ ሆና አጠናቀቀች

ወደ ቡዳፔስት አቅንቶ የነበረው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ከነሀሴ 13 ቀን እስከ 21 ቀን 2015 ዓ.ም በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ሲካሄድ የቆየው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ተጠናቋል። በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ 195 የዓለማችን ሀገራት የተሳተፉ ሲሆን ሜዳሊያ ማግኘት የቻሉ ሀገራት ግን 46 ብቻ ናቸው ተብሏል። ከማጣሪያ ውድድሮች ጀምሮ እስከ ፍጻሜ ድረስ 2 ሺህ 100 አትሌቶች በተሳፉበት በዚህ ውድድር ላይ 50 አትሌቶች የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው ሲያስገኙ 48 የብር እንዲሁም 50 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ተወዳዳሪዎቹ ለሀገራቸው አስገኝተዋል፡፡ ውድድሩን 400 ሺህ ተመልካቾች በአካል ስታዲየም ገብተው ታድመውታል የተባለ ሲሆን ሀንጋሪ ደማቅ እና አይረሴ ውድድር ማዘጋጀቷ ተገልጿል። በዓለም አቀፉ…
Read More
ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን የወርቅና የብር ሜዳሊያ አገኘች

በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት አስተናጋጅነት እየተካሄደ ያለው የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ሰባተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት አማኔ በሪሶ አትሌት ጎቲቶም ገብረ ስላሴ የወርቅ እና ብር ሜዳሊያዎችን አግኝታለች፡፡ ሞሮካዊቷ አትሌት ፋጥማ ጋርዳዲ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቃለች። ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያ ልታገኝባቸው የምትችልባቸው ቀሪ ውድድሮች ያሉ ሲሆን አሁን ላይ በሁለት ወርቅ፣ በአራት ብር እና በሁለት ነሀስ በደምሩ በስምንት ሜዳሊያዎች ከዓለም በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ አሜሪካ በስምንት የወርቅ፣ ስፔን በአራት ወርቅ እንዲሁም ጃማይካ በሶስት የወርቅ ሜዳሊያ ከአንደኛ እስከ ሶተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ እና ነገ በሚካሄዱ የወንዶች ማራቶን፣ በሴቶች እና ወንዶች አምስት ሺህ ሜትር ውድድሮች ላይ የምትሳተፍ…
Read More