ስፖርት

ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

28ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ጨዋታ የሊጉ መሪ የሆነው ቅዱስ ጊዮርጊስን ከኢትዮጵያ ቡና አገናኝቷል። በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ይህ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። እስማኤል ኦሮ አጎሮ ቅዱስ ጊዮርጊስን ቀዳሚ ያደረገች ጎል ሲያስቆጥር ብሩክ በየነ ደግሞ የኢትዮጵያ ቡናን አቻ ያደረገች ጎል አስቆጥሯል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር ከመቻል ጋር እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ተብሏል። ከአራት ቀናት በኋላም ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና፣ አርባምንጭ ከተማ ከድሬዳዋ፣ ወላይታ ዲቻ ከወልቂጤ ከተማ፣ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ መድህን እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ59 ነጥቦች ሲመራ ባህርዳር በ54 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን ደግሞ በ48 ነጥብ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ ከኮቲዲቯሩ የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ ሆነች

ኢትዮጵያ ከኮቲዲቯሩ የአፍሪካ ዋንጫ ውጪ ሆነች

በኮቲዲቯር አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዚህ ማጣሪያ ጨዋታ አንድ አካል የሆነው ጨዋታ ከማላዊ አቻው ጋር አድርጓል። ይህ ጨዋታ ዜሮ ለዜሮ በሆነ አቻ ውጤት የተጠናቀቀ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከኮቲዲቫሩ የአፍሪካ ዋንጫ መውደቁን አረጋግጧል። ምድቡን እየመራች ያለችው ግብጽ አስቀድማ ማለፏን ያረጋገጠች ሲሆን ጊኒ ደግሞ ሁለተኛ በመሆን ለአፍሪካ ዋንጫው ማለፏን አረጋግጣለች። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት ውበቱ አባተ በውጤት ማጣት መሰናበታቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከአሰልጣኝ ውበቱ ጋር በስምምነት እንደተለያየ ከዚህ በፊት አስታውቋል። በያዝነው ዓመት ለሚካሄደው የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጇ ኮቲዲቯርን ጨምሮ ከ15 በላይ ሀገራት ማለፋቸውን አረጋግጠዋል። ኮቲዲቯር፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ደቡብ አፍሪካ፣…
Read More
ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ

ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ

ማንችስተር ሲቲ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አነሳ የጣልያኑ ኢንተርሚላንን እና የእንግሊዙ ማንችስተር ሲቲን ያገናኘው የዘንድሮው የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በሲቲ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ትናንት ምሽት በቱርክ ኢስታምቡል በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ሮድሪጎ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠራት ጎል ማንችስተር ሲቲ ዋንጫውን ማሸነፍ ችሏል፡፡ ማንችስተር ሲቲ በስፔናዊው አሰልጣኝ ፔፔ ጋረዲዮላ አሰልጣኝነት ታግዞ በታሪክ የመጀመሪያውን የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ማንሳት ችሏል፡፡ ማንችሰተር ሲቲ በ2022/23 የውድድር ዓመት ከቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ በተጨማሪ የእንግሊዝን ፕሪሚየር ሊግ እና ኤፍኤካፕ ዋንጫን በማንሳት የሶትዮሽ ዋንጫ መውሰድ ችሏል፡፡ አሰልጣኝ ፔፔ ጋርዲዮላ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ከባርሴሎና፣ ባየርንሙኒክ እና ማንችስተር ሲቲ ጋር አሸንፏል፡፡ ከቦርሲያ ዶርትሙንድ ማንችስተር ሲቲን ከአንድ ዓመት በፊት የተቀላቀለው ኖረዌያዊው አርሊንግ ሀላንድ በ12 ጎሎች…
Read More
ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ደምቀው አምሽተዋል

ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ደምቀው አምሽተዋል

የፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ትናንት ምሽት የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን እና ኬንያዊያን አትሌቶች ድል ቀንያቸዋል። ኢትዮጵያዊው ለሜቻ  ግርማ ለ19 አመት ተይዞ የነበረውን የ3 ሺህ መሰናክል ክብረወሰን በመስበር አሸንፏል። ከውድድሩ አስቀድሞ ሪከርዱን እንደሚሰብር ሲናገር የነበረው ለሜቻ በአንድ ወር ውስጥ ሁለተኛ ክብረወሰኑ ሁኖ ተመዝግቧል ። አትሌቱ 7:51:11 በመግባት ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አብርሃም ስሜ8:10:73 የግሉን ምርጥ  ሰዓት በማስመዝገብ 4ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል ። ከቀናት በፊት የ1500 ሜትር የአለም ክብረ ወሰን የሰበረችው ኬኒያዊቷ ፌዝ ኪፕዮገን ለመጀመሪያ ጊዜ በተዋዳደረችበት የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ለ8 ዓመት ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች። የዚሁ ርቀት ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው እና በውድድሩ ላይ የተሳተፈችው ለተሰንበት ግደይ ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች። የ5 ኪሎ…
Read More
ሊድስ ዩናይትድ እና ሌቺስተር ሲቲ ሳውዛምፕተንን ተከትለው መውረዳቸው አረጋገጡ

ሊድስ ዩናይትድ እና ሌቺስተር ሲቲ ሳውዛምፕተንን ተከትለው መውረዳቸው አረጋገጡ

የ2022/23 የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ፍፃሜውን አግኝቷል። የዘንድሮው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ማንችስተር ሲቲ የዋንጫ አሸናፊ ሲሆን አርሰናል፣ ማንችስተር ዩናይትድ እና ኒውካስትል ከአንደኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል። ሊቨርፑል እና ብራይተን በቀጣይ አመት የዩሮፓ ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ሲያልፉ አስቶን ቪላ የአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ተሳታፊ ሆኗል። የማንችስተር ሲቲው አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ በ36 ግቦች የውድድሩ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ማጠናቀቅ ችሏል። አርሊንግ ሀላንድ ከኮኮብ ግብ አግቢነት በተጨማሪ የእንግሊዝ ኮኮብ ተጫዋች እና ወጣት ተጫዋች ሽልማትንም አሸንፏል። ሳውዝሀምፕተን ፣ ሊድስ ዩናይትድ እና ሌስተር ሲቲ ወደ እንግሊዝ ሻምፒዮን ሺፕ መውረዳቸውን ያረጋገጡ ክለቦች ሆነዋል። በቀጣይ የውድድር አመት ሉተን ታውን ፣ ሼፍልድ ዩናይትድ እና በርንሌይ ወራጅ ክለቦችን…
Read More
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ፡፡ ከሁለት ጨዋታዎች በፊት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሀ የከፍተኛ ሊግ ውድድር የመዝጊያ ስነ-ሥርዓት ላይ ዋንጫውን አንስቷል፡፡ ቡድኑ ቀሪ የመርሐ ግብር ጨዋታውን ከቀኑ 6፡00 ላይ ከሰንዳፋ በኬ ጋር በማድረግ 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፎ ነጥቡን 60 ማድረስ ችሏል፡፡ በውድድሩ የመዝጊያ መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመርቻንት እና ኤጀንት ባንኪንግ ዳይሬክተር አቶ ብሌን ኃ/ሚካኤል እና ሌሎች እንግዶች ለሻምፒዮኑ ቡድን እና ለሌሎች ተሸላሚዎች…
Read More
ማንችስተር ሲቲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን አሸነፈ

ማንችስተር ሲቲ የዘንድሮውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን አሸነፈ

አጓጊው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ ቀርቶታል። ማንችስተር ሲቲ ቀሪ ሁለት ጨዋታ እየቀረው የ2022/23 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን አሸንፏል። የዘንድሮውን ውድድር ሳይጠበቅ ለረጅም ወራት ሲመራ የቆየው አርሰናል ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ እርግጥ ሆኗል። አርሰናል በትናንትናው ዕለት ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረገውን ጨዋታ መሸነፉን ተከትሎ በፔፔ ጋርዲዮላ የሚሰለጥነው ማንችስተር ሲቲ ሁለት ጨዋታዎች እየቀሩት ዋንጫ መብላቱን አረጋግጧል። ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ለማለፍ የሚደረገው ትንቅንቅ እንደቀጠለ ሲሆን ሊቨርፑል በአስተንቪላ መሸነፉ የተሳትፎ ተስፋውን አክስሟል። ከቦርንማውዝ የተጫወተው ማንችስተር ዩናይትድ በካዝሚሮ ብቸኛ ጎል ማሸነፉን ተከትሎ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ተስፋውን የበለጠ አለምልሟል። ከፕሪሚየር ሊጉ ላለመውረድ እየተደረገ ያለው ትንቅንቅ የቀጠለ ሲሆን ሳውዛምፕተን ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱን አረጋግጧል። ሊድስ ዩናይትድ፣…
Read More
ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተርሚላን ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተርሚላን ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

በአውሮፓ ምርጥ እግር ኳስ ክለቦች ሙካከል ሲካሄድ የቆየው የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ተፋላሚዎች ታውቀዋል። ትናንት ምሽት በእንግሊዝ ማንችስተር ከተማ በሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ መካከል የተካሄደው ውድድር በሲቲ የበላይነት ተጠናቋል። በርናርዶ ሲልቫ ሁለት ጎል፣ አልቫሬዝ እና ሚሊታኦ በራሱ ግብ ላይ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ሲቲ በቱርክ ኢስታምቡል ከተማ ለሚካሄደው የፍጻሜ ውድድር ማለፍ ችሏል። የጣልያኑ ኢንተር ሚላን በፍጻሜው ማንችስተር ሲቲን የሚገጥም ሲሆን ጨዋታው ሰኔ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት 4:00 ላይ ይካሄዳል ተብሏል። የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ውድድርን የስፔኑ ሪያል ማድሪድ 14 ጊዜ በማሸነፍ ቀድሚው ክለብ ሆኖ ተመዝግቧል። የፍጻሜ ተፋላሚው ማንችስተር ሲቲ እስካሁን አንድም ጊዜ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግን ያላሸነፈ ሲሆን ሌላኛው የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተርሚላን ሶስት…
Read More
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ተሾመ

ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ተሾመ

ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ቡድኑን በጊዜያዊነት የሚመሩ አሰልጣኞችን ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ቡድኑን ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲመሩ ከቆዩት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ጋር በስምምነት ከተለያየ በኋላ ቀጣዩን አሰልጣኝ ለመምረጥ የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውይይት ማድረጉን ገልጿል። በዚሁ መሰረት ኮሚቴው በቴክኒክ ዳይሬክተርነት እየሰሩ የሚገኙትን ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት ቀጣይ ጨዋታዎችን እንዲመሩ ከውሳኔ ላይ መድረሱን አመልክቷል። በተጨማሪ ኮሚቴው ኢንስትራክተር ዳንኤልን እንዲያግዙ በፕሪምየር ሊጉ በመስራት ላይ የሚገኙትና በወቅታዊ ውጤታማነት የተሻሉ ሆነው ተገኝተዋል ያላቸውን የባህር ዳር ከተማ አሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው ምክትል አሰልጣኝ ሆነው እንዲሰሩ መወሰኑን ጠቅሷል። ፌዴሬሽኑ…
Read More
ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመቻል ተሸነፈ

ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመቻል ተሸነፈ

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቻል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል። የመቻልን የማሸነፊያ ግብ የቀድሞ የፈረሰኞቹ ተጨዋች ከነዓን ማርክነህ በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። ፈረሰኞቹ በዛሬው ጨዋታ ሙሸነፋቸውን ተከትሎ በውድድር አመቱ ሁለተኛ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል። የቀድሞው መከላከያ እግር ኳስ ክለብ የአሁኑ መቻል ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 33 በማድረስ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሽንፈት ያስተናገደው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ51 ነጥብ ሊጉን እየመራ ይገኛል። የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሽንፈት ማስተናገዱን ተከትሎ ከተከታዩ ባህርዳር ከተማ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ጠቧል። በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሀዋሳ ከተማ እንዲሁም መቻል ከ ሲዳማ…
Read More