ኪነ ጥበብ

ዲኤስቲቪ በአንጋፋው የአፍሪካ መዝናኛ ፕሮግራም መሪ ኖሎ ሌተሌ ላይ ያተኮረ አዲስ ዘጋቢ ፊልም ሊያሳይ ነው

ዲኤስቲቪ በአንጋፋው የአፍሪካ መዝናኛ ፕሮግራም መሪ ኖሎ ሌተሌ ላይ ያተኮረ አዲስ ዘጋቢ ፊልም ሊያሳይ ነው

አፍሪካ በአለምአቀፍ የብሮድካስት መዝናኛ ኢንደስትሪ ውስጥ ያላትን ቦታ እንዲረጋገጥ ባለፉት 50 ዓመታት የተሰሩ እንቅስቃሲዎች ላይ ትኩረቱን ያደረግውና በተለይም የቀድሞ የመልቲቾይስ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ በመሆን ለረጅመ ጊዜ ያገለገሉት ኖሎ ሌተሌ አስተዋዎ የሚቃኝው አዲስ ዘጋቢ ፊልም “አዎ ለማይቻለው፣ የኖሎ ሌተሌ ታሪከ ” በሚል ርዕስ ተዘጋጀቶ ለእይታ ሊበቃ ነው፡፡  ዘጋቢ ፊልሙ በመላው አፍሪካ ነፃነት ለማግኘት የሚደረጉ እንቅስቃሲዎች በተንሰራፋበት ወቅት በታዳጊ ዕድሚ ላይ የነበሩት ኖሎ አህጉሪቱ የራሷ የሆነ ድምጽ እንዲኖራት የነበራቸውን ራዕይ እንዴት እንደቀረፁት ፣ ይህንንም ራዕይ እውን ለማድረግ ሲያደርጉት የነበረውነ ያላሰለሰ ጥረት እና ረጅም ጉዞ በጥልቀት የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ነው፡፡ በሳውዝሃምፕተን ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሪከ ምህንድስና ትምህርት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በዚያን ጊዜ የአፓርታይድ ስርዓት የምትከተለው…
Read More
መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን ለተመልካቾቹ አቀረበ

መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን ለተመልካቾቹ አቀረበ

ከመልቲቾይዝ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የሆነው ዲኤስቲቪ ለኢትዮጵያ ተመልካቾች የተለያዩ መዝናኛ ፕሮግራሞችን በማቅረብ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ድርጅቱ በትናንትናው ዕለት ባዘጋጀው ፕሮግራም ከዚህ በፊት የነበሩ እና በቀጣይ ስለሚጀመሩ አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራሞቹን አስተዋውቋል፡፡ በመድረኩ ላይ አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ተጽዕኖፈጣሪ ሰዎች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ የመልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ቁጥጥር እና ኮርፖሬት ሃላፊ አቶ መታሰቢያ በላይነህ በመድረኩ ላይ እንዳሉት መልቲቾይዝ ኢትዮጵያ ለደንበኞቹ በየጊዜው አዳዲስ የመዝናኛ ፕሮግራም እና ይዘቶችን ያቀርባል ብለዋል፡፡ ድርጅቱ በዚህ ወቅት እንዳለው ከዚህ በፊት ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ሲያቀርባቸው ከነበሩት የመዝናኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪ አዳዲስ ይዘቶችን እንደሚያቀርብ ገልጿል፡፡ በድርጅቱ በኩል ለኢትዮጵያ ተመልካቾች ይቀርቡ ከነበሩት ይዘቶች በተጨማሪ አዳዲስ ፕሮግራሞችን በአማርኛ እና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች የሚተላለፉ ይዘቶች…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የድምጻዊ አማኑኤል ሙሴ (ዝናር ዜማ) አልበምን ስፖንሰር አደረገ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የድምጻዊ አማኑኤል ሙሴ (ዝናር ዜማ) አልበምን ስፖንሰር አደረገ

ሰዋሰዉ መልቲሚዲያ እና ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ በሙዚቃዉ ዘርፍ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። ከ100 በላይ አንጋፋና ወጣት ድምፃዉያንን እና ሙዚቀኞችን ያስፈረመው ሰዋሰዉ መልቲሚዲያ እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሙዚቃ አልበሞች እና በሁነቶች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተፈራርመዋል። ከሰዋሰዉ ድምፃዉያን መካከል አንዱ የሆነዉ እና ከፋሲካ ፆም በኋላ የሚለቀቀዉን የአማኑኤል ሙሴ አልበም ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የስፖንሰርሺፕ ድርሻዉን ወስዷል። በዝናር ዜማ የድምፃዉያን ስብስብ እራሱን ከህዝብ ጋር ያስተዋወቀዉ አማኑኤል ሙሴ  ‘’ጥቁር ዉሃ’’ የተሰኘዉ አልበሙም በሳፋሪኮም አጋርነት በሰዋሰዉ አፕ እንደሚለቀቅ ተገልጿል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከአማኑኤል ሙሴ በተጨማሪ ተስፋ የሚጣልባት ወጣት ሴት ድምፃዊ አልበምን ስፖንስር እንደሚያደርግ የተነገረ ሲሆን የድምፃዊቷን ማንነት ግን በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሏል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙዚቃ አልበምን ስፖንሰር ሲያደርግ የአሁኑ…
Read More
አቦል ቴሌቪዥን “ዳግማዊ” እና “ቁጭት” የተሰኙ አዲስ ተከታታይ ድራማዎችን ማስተላለፍ ሊጀምር ነው

አቦል ቴሌቪዥን “ዳግማዊ” እና “ቁጭት” የተሰኙ አዲስ ተከታታይ ድራማዎችን ማስተላለፍ ሊጀምር ነው

አቦል ቴሌቪዥን ከሰኞ ህዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሁለት አዳዲስ “ሀገርኛ” ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማዎችን ለተመልካቾቹ ላቀርብ ነው ብሏል፡፡ ለተመልካቾች የሚቀርቡት “ቁጭት” የተሰኘው ረጅምና ወጥ ሀገርኛ ተከታታይ ቴሌኖቬላ እና “ዳግማዊ” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው ድራማ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ይዘቶች አቦል ቴሌቪዥን ለደንበኞቹ ምርጥ ወጥ ሀገርኛ ይዘቶችን ለማቅረብ የወጠነውን ጅምር በተግባር የሚያረጋግጡና ቻናሉ የላቁ መዝናኛዎችን ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ናቸው። “ቁጭት” የተሰኘው ሀገርኛ ቴሌኖቬላ ታሪኩ የሚያጠነጥነው በሕይወት ጥቂት ወራት ብቻ እንደሚቀረው ከተነገረው በኋላ የናፈቀውን ልጁን ዮናስን ለማግኘት ፍለጋ በጀመረ አባት ነው፡፡ ድርጊቱ በተስፋ ማጣት እና በድህነት ውስጥ ያለን የሕይወት ውጣውረድም የሚያስቃኝ ሲሆን ዮናስ የአባቱን ህልውና እና ባለጸጋነት ታሪክ ሳያውቅ ሕይወቱ…
Read More
ብሪታንያ ከመቅደላ የዘረፈቻቸውን ቅርሶች ለኢትዮጵያ አስረከበች

ብሪታንያ ከመቅደላ የዘረፈቻቸውን ቅርሶች ለኢትዮጵያ አስረከበች

ከመቅደላ ተዘርፈው የተወሰዱ የተለያዩ የኢትዮጵያ ቅርሶች በለንደን ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተመለሱ በ1868 በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት በብሪታንያ ተዘርፈው የተወሰዱ የኢትዮጵያ ቅርሶች መመለሳቸውን በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡ ከተመለሱት ቅርሶች መካከል በ1868 ዓ.ም ከመቅደላ የተዘረፈ የመድሃኒያለም ታቦት፣ የልኡል አለማየሁ የጸጉር ዘለላ፣ ከብር የተሰሩና በነሃስ የተለበጡ ሦስት ዋንጫዎች እንዲሁም በዘመኑ ጦርነት ላይ የዋለ የጦር ጋሻ እንደሚገኙበት ገልጿል፡፡ ለንደን በሚገኘው የአቴናየም ክለብ በተካሄደው የቅርሶቹ ርክክብ ሥነ ስርዓት ላይ፤ በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ልኡካን ቡድን፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ፣ የብሪታኒያ ፓርላማ አባላት፣ ቅርሶቹን ለማሰመለስ የተባበሩ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመርሀ ግብሩ ላይም አምባሳደር ተፈሪ መለሰ፤ የተመለሱት የተለያዩ…
Read More
ሸራተን ሆቴል የድምጻዊ ሬማ አዲስ ዓመት ዋዜማ ኮንሰርትን ሰረዘ

ሸራተን ሆቴል የድምጻዊ ሬማ አዲስ ዓመት ዋዜማ ኮንሰርትን ሰረዘ

የ2016 አዲስ ዓመትን አስመልክቶ በሸራተን አዲስ ሆቴል የሙዚቃ ድግስ መዘጋጀቱን የሚገልጹ ማስታወቂያዎች ሲተላለፉ ሰንብተዋል፡፡ በዚህ የአዲስ ዓመት ዋዜማ ላይ የሙዚቃ ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ድምጻዊያን የማስታወቂያው አንድ አካል የነበሩ ሲሆን ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድምጻዊያን ጋር በመድረኩ ላይ እንደሚዘፍኑ ተገልጾም ነበር፡፡ ይሁንና ድምጻዊ ሬማ ከክርስትና ሀይማኖት ጋር በተያያዘ ያልተገባ ነገር አድርጓል በሚል ይህን የአዲስ ዓመት ዋዜማ የሙዚቃ ድግስ ላይ ላለመገኘት በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ ቅስቀሳ ሲደረግ ሰንብቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም በይፋ የቤተ ክርስቲያን በዓላት ሲደርሱ ከሥርዓቷ እና ከአስተምሮዋ ውጪ በ ሆነ መልኩ የተለያዩ አካላት የዳንኪራ ጥሪ በማዘጋጀት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አግባብነት የሌለው መሆኑን…
Read More
አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

አርቲስቶች እና ስፖንሰሮች የአዲስ ዓመት ዋዜማ ሙዚቃ ኮንሰርቶችን ሰረዙ

ኢትዮጵያ የ2016 አዲስ ዓመትን ከአምስት ቀናት በኋላ የምታከብር ሲሆን በበዓሉ ዋዜማ የሙዚቃ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። የአዲስ ዓመት ዋዜማ ዕለት ከሚዘጋጁ የሙዚቃ ድግሶች መካከል በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል የተዘጋጀው አንዱ ነበር። በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የውጭ ሀገራት እና ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ማስታወቂያዎች በሚዲያዎች በመተላለፍ ላይ ናቸው። ናይጀሪያዊው ዲቫይን ኢኩቦር ወይም በቅጽል ስሙ ሪማ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ፣ ከሀገር ውስጥ ደግሞ ልጅ ሚካኤል፣ ኩኩ ሰብስቤ እና ሌሎችን ድምጻዊያን በዚህ የአዲስ ዓመት ኮንሰርት ላይ የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጾ ነበር። ይሁንና ድምጻዊ ሬማ የክርስትና እምነት ላይ ከዚህ በፊት አሹፏል በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች በዚህ ኮንሰርት ላይ እንዳይገኙ መልዕክት ማስተላለፏን ተከትሎ በርካቶች…
Read More
የሞስኮ ትምህርት ቤቶች በሚቀጥለው ሳምንት አማርኛ እና ስዋህሊ ቋንቋን ማስተማር እንደሚጀምሩ ገለጹ

የሞስኮ ትምህርት ቤቶች በሚቀጥለው ሳምንት አማርኛ እና ስዋህሊ ቋንቋን ማስተማር እንደሚጀምሩ ገለጹ

ሩሲያ ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ ከመስከረም ወር ጀምሮ አማርኛ እና ስህዋህሊ ቋንቋዎችን በሞስኮ በሚገኙ በአራት ትምህርተ ቤቶች ማስተማር እንደምትጀምር ገልጻ ነበር። በዚህም መሰረት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ መስከረም በሞስኮ የሚገኙ ትምህ ቤቶች የአፍሪካ ቋንቋዎችን ማስተማር ይጀመራል ሲል የሞስኮ ትምህርት እና ሳይንስ ክፍል አስታውቋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል። እንደ ዘገባው ከሆነ 1517 የተሰኘው የፔዳጎጂ ትምህርት ቤት ስዋህሊ ቋንቋን ሁለተኛው የውጭ ቋንቋ አድርጎ ያስተምራል ተብሏል። እንዲሁም 1522 የተሰኘው ትምህርት ቤት ደግሞ አማርኛ ቋንቋን እንደሚያስተምር ተገልጿል። ሩሲያ የአፍሪካ እና ሞስኮን ወዳጅነት ለማጠናከር በሳምንት አንድ ወይም ሁለት የትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ለአፍሪካ ቋንቋዎች ማስተማሪያ እንዲውሉ ይደረጋል ብላለች። ሩሲያ በቀጣይም በምዕራብ አፍሪካ ሰፊ ተናጋሪ ያለው ዩርባ ቋንቋን ማስተማር…
Read More
ድምጻዊ አቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበሙን በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ ተከለከለ

ድምጻዊ አቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበሙን በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ ተከለከለ

በኦሮሚኛ እና አማርኛ የሙዚቃ ስራዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ አቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበም ለቋል። "እንዳባቴ እወድሻለሁ" በሚል ለገበያ ያቀረበው ይህ የአቡሽ ዘለቀ አዲስ አልበም በገበያ ላይ በመሸጥ ላይ መሆኑን አስታውቋል። ድምጻዊው በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳለው ምክኒያቱ ባልተገለጸበት ሁኔታ አልበሜ በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ መከልከሉን ገልጿል። "እንደ አባቴ እወድሻለሁ" የተሰኘዉ አልበም በማህበራዊ መገናኛ መንገዶች ላይ በይፋ የተለቀቀ ቢሆንም በአዲስ አበባ ሲዲዉን የሚያዞሩ ወጣቶች መሸጥ እንዳይችሉ በፖሊስ መከልከላቸውንም ጠቅሷል። በትናንትናው እለት ሲዲዉን ለመሸጥ የወጡ ወጣቶች ከተከለከሉ በኋላም ድምፃዊዉ ክልከላዉ ለምን እንደተላለፈ አላዉቅም ብሏል። ድምፃዊዉ "ሁሉም ሰዉ ለኔ እኩል ነዉ ፤ በእኩልነት በአብሮነት ፣ በአንድነት የማምን ሰዉ ነኝ ያንን ሀሳብ ነዉ በአልበሜ ላይ ለማንጸባረቅ የሞከርኩት" ብሏል።…
Read More
አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አርቲስት አብነት ዳግም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በበርካታ ቴአትሮች ፣ ፊልሞች እና የቴሌቭዥን ድራማዎች ላይ በተዋናይነት በመሳተፍ እውቅናን ያተረፈው አርቲስት አብነት ዳግም በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ አርቲስት አብነት ለረዥም ጊዜ በከባድ የስኳር በሽታ ታምሞ የቆየ ሲሆን፤ ትናንት ሕመሙ በርትቶበት ወደ ጤና ጣቢያ ቢወሰድም ሕይወቱን ማዳን ሳይቻል በመቅረቱ ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል፡፡ አርቲስት አብነት አሉላ አባነጋ፣ የቼዝ ዓለም፣ ዳኛው፣ እስረኛው ንጉስ እና ነቅዕ ቴአትሮች ላይ ተውኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አያስቅም፣ አንድ እድል፣ ላምባዲና፣ ሰበበኛ፣ ባንቺ የመጣ፣ ቁልፉን ስጭኝ፣ የነገርኩሽ እለት፣ ፍቅር እስከ መቃብር እና አትሸኟትም ወይ በተሰኙ ፊልሞች ላይ በመተወን አድናቆትን አግኝቷል። ስንቅ ፣መለከት፣ ትርታ እና ለወደዱት ደግሞ የተሳተፈባቸው ቲቪ ድራማዎች ሲሆኑ፤ በግሉም የቅብብሎሽ ድራማን ደርሷል።
Read More