ኢኮኖሚ

ኢትዮ ቴሌኮም የ30 ቢሊዮን ብር አክስዮኑን ለሽያጭ አቀረበ

ኢትዮ ቴሌኮም የ30 ቢሊዮን ብር አክስዮኑን ለሽያጭ አቀረበ

የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻ ሽያጩን በይፋ አስጀምሯል፡፡ 100 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ሀብት ያለው ኢትዮ ቴሌኮም የ30 ቢሊዮን ብር አክስዮኑን ለሽያጭ አቅርቧል፡፡ አንዱን የድርጅቱን አክስዮን ዋጋ በ300 ብር እንደሚሸጥ ያስታወቀው ኢትዮ ቴሌኮም አንድ ግለሰብ መግዛት የሚችለው 33 አክስዮን ወይም 9 ሺህ 900 ብር ነው ተብሏል፡፡ በአጠቃላይ ኢትዮ ቴሌኮም 3 ሺህ 333 አክስዮኖቹን ለሽጭ ያቀረበ ሲሆን 30 ቢሊዮን ብር ከአክስዮን ሽያጭ ለማግኘት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ዜጎች አክስዮን መግዛት ይችላሉ የተባለ ሲሆን ተቋማት ግን አክሲዮንን መግዛት እንደማይችሉ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ፍሬህይወት ታምሩ ተናግረዋል፡፡ የአክሲዮን ሽያጩ ከዛሬ ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይጠናቀቃልም…
Read More
የኢትዮጵያ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫን እንዲያጠቡ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫን እንዲያጠቡ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከውጭ ምንዛሪ ግብይት ጋር በተያያዘ ስለሚፈጸሙ ክፍያዎች የማሻሻያ ፖሊሲ ይፋ አድርጓል:: ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኗን ተከትሎ ባንኮች በየእለቱ የውጭ ምንዛሬ ተመን ይፋ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በዚህም ባንኮች በየእለቱ በሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ የዋጋ ተመን ላይ በመግዣ እና በመሸጫው መካከል ከ10 በላይ ልዩነት ሲታይበት ቆይቷል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫው፤ አዲሱ የምንዛሬ ተመን አሰራር ይፋ መሆኑን ተከትሎ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ ያሉ ሂደቶችን ሲከታተል መቆየቱን አስታውቋል። ብሔራዊ ባንክ የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት በዓለም አቀፍ አሰራር መሰረት መሆን እንዳለበት አመልክቷል። በመሆኑም የውጭ ምንዛሬ መግዣና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት…
Read More
ሀይኒከን ኩባንያ አራዳ ቢራን ጠቀለለ

ሀይኒከን ኩባንያ አራዳ ቢራን ጠቀለለ

የአራዳ መጠጥ ምርቶች አቅራቢ የሆነው ኮማሪ ቤቭሬጅ ለሃይኒከን መሸጡ ተገልጿል፡፡ በአጭር ጊዜ በተጠቃሚዎች ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘው የአራዳ መጠጦች አምራች ኮማሪ ፋብሪካውን ለሃይኒከን ለመሸጥ ሲያደርግ የነበረው ድርድር ከሳምንት በፊት አጠናቋል ተብሏል፡፡ የሽያጩ ድርድር ለበርካታ ወራት ሲደረግ ነበር የተባለ ሲሆን ሁለቱ ወገኖች በሀምሌ ወር ወደ መጨረሻ የድርድር ምእራፍ ቢሸጋገሩም ሀምሌ 22 ቀን 2016 ዓም ወደ ትግበራ የገባውን የምንዛሬ ገበያ ለውጥ ተከትሎ ድርድሩ በድጋሚ ሲደረግ እንደነበር ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ የሽያጩ ዋጋ በዚህ ወር መጨረሻ በይፋ ይገለጻል የተባለ ሲሆን ሁለቱ ወገኖች በዚሁ ወቅት በይፋ ፋብሪካውን እንደሚረካከቡ ተገልጿል፡፡ ኮማሪ ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ 96 ኪሜ ርቀት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጨኬ አካባቢ በገነባው ፋብሪካ…
Read More
ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

በ2010 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ነበር ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ለ20 ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን ግንኙነት ያደሱት፡፡ ሁለቱ ሀገራት የመደበኛ የስልክ አገልግሎትን ዳግም ካስጀመሩ ከሰባት ዓመታት በኋላ ተቋርጧል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሐምሌ 2010 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ሲሰራ የነበረ ሲሆን ከትናንት በስቲያ ማለትም ከመስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንደተቋረጠ በኢትዮጵያ ከሚኖሩ ኤርትራዊያን ሰምተናል፡፡ ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራዊ ለአል-ዐይን እንዳሉት “ከማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መደበኛ ስልክ መደወል አልቻልኩም” ብለዋል፡፡ በኤርትራ ኢንተርኔት አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቦቻችንን የምናገኘው በመደበኛ ስልክ ብቻ ነበር የሚሉት እኝህ አስተያየት ሰጩ አገልግሎቱ መቋረጡ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡ “ቀስ በቀስ የኢትዮጵያ እና…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት እና ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

ለፍልስጤም ነጻነት የሚታገለው ሐማስ በእራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት አንድ ዓመት ሞልቶታል፡፡ ይህ ጦርነት ወደ ሊባኖስ መስፋፋቱን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በርካታ ዓለማችን አየር መንገዶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጓቸውን በረራዎች አቋርጠዋል፡፡ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ወደ ቤይሩት እና ወደ ቴልአቪቭ የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጡን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል። አየር መንገዱ በድረገ ገጹ ባጋራው መረጃ ተለዋጭ ማስታወቂያ እስከሚያወጣ ድረስ ወደ ቤይሩት የሚያደርጋቸውን ሁሉንም በረራዎች ማቋረጡን ገልጿል። ወደ ቴልአቪቭ ደግሞ እስከ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በረራ የማያደርግ መሆኑን ነው አየር መንገዱ የገለጸው። በተጠቀሱት አካባቢዎች ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የጠቀሰው አየር መንገዱ፤ ስለጉዳዩ…
Read More
በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመዋል፡፡ ስምምነቱ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን በውጭ ሀገር በሥራ የሚሰማሩ ዜጎችን መብት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ነው፡፡ በስምምነቱ ወቅት የፌዴሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ፣የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በፊርማው ሥነ-ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ኮንፌዴሬሽኑ በሀገር ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች መብቶች እንዲከበሩ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡ ከሀገር ውስጥ በተጨማሪም በውጭ ሀገራት ተቀጥረው የሚሠሩ ኢትዮጵያዊን መብታቸው ተጠብቆ እዲሠሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ…
Read More
አቶ አንዷለም አድማሴ ሳፋሪኮምን ተቀላቀሉ

አቶ አንዷለም አድማሴ ሳፋሪኮምን ተቀላቀሉ

የኢትዮ ቴሌኮም የቀድሞው ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አንዷለም ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ተቀላቅለዋል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እንዳስታወቀው የቀድሞውን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አንዷለም አድማሴን የውጭ ግንኙነት ሃላፊው ሆነው መሾማቸውን አስታውቋል። አንዷለም የኩባንያው የውጭ ግንኙነት ሃላፊ ኾነው የተሾሙት፣ የቀድሞው ሃላፊ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ ሻወል ከኩባንያው ለቀው ቦይንግ ኩባንያን መቀላቀላቸውን ተከትሎ ነው። አንዷለም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ከሌሎች ግለሰቦች ጋር ያቋቋሙትን አንድ አዲስ የቴሌኮም ኩባንያ በሃላፊነት በመምራት ላይ ነበሩ:: ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የቴሌኮም አገልግሎት ነሀሴ 2014 ዓ.ም ላይ በድሬዳዋ ማስጀመሩ ይታወሳል፡፡ ድርጅቱ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለ50 በመቶ ህዝብ እንዲሁም በቀጣዮቹ አስር ዓመታት ውስጥ ደግሞ 98 በመቶ ለሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የቴሌኮም አገልግሎት…
Read More
የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኙት በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በሀገሪቱ እያጋጠመን ይገኛል ባሉት ተግዳሮቶች ወደ ጎረቤት ሀገራት እየሄዱ መሆኑን ገለፁ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ ቀዳሚ የሆኑት የቻይና ባለሀብቶች እና ኩባንያዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ ሌሎች ሀገራት እየተሰደዱ መሆኑን ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑት የቻይና ባለሃብቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያጋጠማቸው በመንግስት አመቺ የስራ ሁኔታዎች እየተሰጠ ባለመሆኑ ወደ ጎሮቤት ሃገራት ማለትም ወደ ኬንያ ፣ ኡጋንዳ እንዲሁም ታንዛኒያ እያማተሩ እንደሚገኙ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ተወካይ እንደተናገሩት በብዙ ምክንያቶች ቻይናውያን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን ንግዳቸውን ወደ ጎሮቤት አገሮች አዙረዋል ። "ይህ ለኤምባሲው ብቻ ሳይሆን ለሀገርም ትልቅ ስጋት ነዉ ምክንያቱም የእኛ ተልዕኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለዉን ትብብር…
Read More
ኢትዮጵያ ግዙፉን የሲሚንቶ ፋብሪካ አስመረቀች

ኢትዮጵያ ግዙፉን የሲሚንቶ ፋብሪካ አስመረቀች

አዲሱ የሲሚንቶ ፋብሪካ በቀን አንድ መቶ ሃማሳ ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ የማምረት አቅም አለው ተብሏል፡፡ ፋብሪካው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል፡፡ ፋብሪካው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ልዩ ቦታው ለሚ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የተገነባ ሲሆን ፋብሪካው ከአዲስ አበባ በ134 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። ተገንብቶ ለመጠናቀቅ ሁለት አመታትን ብቻ የወሰደው ፋብሪካ ዘመናዊ የሆነ ከሰው ንክኪ የራቀ ቴክኖሎጂ የሚጠቀም በመሆኑ የበለጠ ምርት ለማምረት የቀነሰ ኃይል የሚያስፈልገው ነው ተብሏል። በተለይም 174 ሜትር ርዝመት ያለው በአለም ረዥሙ የሆነውን የቅድመ ማሞቂያ ማማ እንደያዘ በምረቃው ወቅት ተገልጿል። የፋብሪካው የማምረት አቅም ከዚህ በፊት በማምረት ላይ ያሉ ተመሳሳይ ፋብሪካዎች ተደምረው የሚያመርቱትን ሃምሳ…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ማስተላለፍ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ማስተላለፍ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ

ኩባንያው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ለዘመድ አዝማድ የሚልኩትን ገንዘብ (ሪሚታንስ) በማስተላለፍ አገልግሎት ላይ ለመሠማራት ማቀዱን አስታውቋል። ኩባንያው በዘርፉ መሠማራት የፈለገው፣ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ለውጡ በመደበኛውና በትይዩ ገበያው መካከል ያለውን የምንዛሬ ልዩነት ማጥበቡን ተከትሎ ነው ኩባንያው፣ ኬንያና ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሪሚታንስ አስተላላፊነት ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን ከዓለማቀፉ ገንዘብ አስተላላፊ ኩባንያ ዳሃብሺል ጋር ባለፈው ሐምሌ የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል። የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት የሆነው ኤምፔሳ (M-PESA) ከአንድ ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የአገልግሎት ፍቃድ ካገኘ ከሦስት ወራት በኋላ ስራ መጀመሩ አይዘነጋም። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለኔትወርክ ማስፋፊያ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መድቤያለሁ ብሏል፡፡ ተቋሙ አክሎም በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎችበተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ…
Read More