መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት ከአበባ ኤክስፓርት ከ 3 መቶ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች፡፡ የሆርቲካልቸር ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም የአበባ ኤክስፖርት ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከፍተኛ አስተዋጽኦን  እያበረከተ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ምርት ግብይት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ አበበ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት 79 ሺህ 819 ቶን የአበባ ምርት ለውጪ ገበያ በማቅረብ 392 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ አግኝታለች ብለዋል። የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአብዛኛው ወደ አውሮፓና ኤዥያ ሀገራት እንደሚላክ  የተናገሩት   ስራ አስፈፃሚው  ምርጥ አስር ተብለው ከተለዩት ተቀባይ ሀገራት መካከል ደግሞ ኔዘርላንድ ትልቁን ድርሻ ትይዛለች ብለዋል።  በበጀት አመቱ አስር ወራት ከእቅድ አፈፃፀም አንጻር ሲታይ የተገኘው ገቢ…
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይትን ማስቆም እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይትን ማስቆም እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከወርቅ ማዕድን 363 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ያቀደች ቢሆንም የተገኘው ግን 67 በመቶው ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይት ዋነኛው ችግር መሆኑን ተከትሎ በመከላከያ ኮማንድ ፖስትና በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጭምር ክትትል ቢደረግም ህገ ወጥ የወርቅ ንግድን ማስቆም እንዳልተቻለ ማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በማዕድናት ሕገ ወጥ ግብይት፣ ኮንትሮባንድና የፀጥታ ችግር ምክንያት በባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ ብሔራዊ ባንክ የገባው ወርቅ ሦስት ቶን ብቻ እንደሆነ፣ ይህም ከዕቅዱ 50 በመቶ ብቻ መሆኑ ታውቋል፡፡ በመጋቢት ወር ብሔራዊ ባንክ የገባው ወርቅ 350 ኪሎ ግራም ሲሆን ይህም በ2014 መጋቢት ወር ከተገኘው 800 ኪሎ ግራም በእጅጉ ያነሰ ነው ተብሏል፡፡ በአገሪቱ ያሉ ወርቅ…
Read More
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 10 ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 10 ሰዎች መገደላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት መንግስት ታህሳስ እና ግንቦት ላይ በፈጸማቸው ሁለት የድሮን ጥቃቶች 10 ሰዎች ሲገደሉ ከ10 በላይ ቆስለዋል ብሏል፡፡ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ በአፋር፣ በሶማሊ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ባወጣው የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ሲሆን አሁንም ከሕግ ውጭ ግድያ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ፣ የዘፈቀደ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፣ አስገድዶ መሰወር፣ እገታ፣ እና የሀገር ውስጥ መፈናቀል እጅግ አሳሳቢ ሆነው የቀጠሉ የመብት ጥሰቶች መሆናቸው ተገልጿል። ኮሚሽኑ በጸጥታ ችግር እና ከመንግስት ተገቢውን ትብብር ባለማግኘት እንዲሁም በሌሎች ምክንያቶች…
Read More
መንግስት በአማራ ክልል የጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲያነሳ ተጠየቀ

መንግስት በአማራ ክልል የጣለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲያነሳ ተጠየቀ

የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በኢትዮጵያ እንደ አዲስ እየተባባሱ የመጡት የሲቪክ ምህዳሩን የሚያጣብቡ ድርጊቶች እንዳሳሰቡት አስታውቋል። የፌደራል መንግሥት ከአንድ ዓመት በፊት የክልል ልዩ ሀይሎችን “መልሼ አደራጃለሁ” የሚል ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው። ግጭቱ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና የፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተካሄደ ሲሆን ግጭቱ ተባብሶ መቀጠሉን ተከትሎ በአማራ ክልል ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ ይታወሳል። ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የታወጀው ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት የተራዘመ ሲሆን ይህ አዋጅ ሊጠናቀቅ ሶስት ሳምንታት ቀርቶታል። ይኼውም የጸጥታ እና ደህንነት አካላት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ምርመራ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን እያዋከቡ ከመሆኑንም ባሻገር በቲያትር እና…
Read More
አምባሳደር ሌንጮ ባቲ የአሜሪካ አምባሳደር ተደርገው ሊሾሙ ነው ተባለ

አምባሳደር ሌንጮ ባቲ የአሜሪካ አምባሳደር ተደርገው ሊሾሙ ነው ተባለ

በዋሸንግተን የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ስለሺ በቀለ የስልጣን መልቀቂያ አስገብተዋል በአሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሌንጮ ባቲ አምባሳደር ሽለሺን ይተካሉ ተብሏል በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ ያቀረቡት መልቀቂያ ተቀባይነት ማግኘቱ ተሰማ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት የቀድሞው የውኃ ሀብት ሚኒስትር ስለሺ በቀለ  ከተሾሙበት የመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ለመልቀቅ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ምንጮች ገለጹ። ስለሺ በቀለ  በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደርነት ሹመታቸው ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ከመንግሥት መዋቅር በመልቀቅ በግል ተቀጥረው በሙያቸው ለማገልገል ማቀዳቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። አምባሳደር ስለሺ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሥልጣን ዘመን ወቅት የፓርቲ አባል ሳይሆኑ የመንግሥት መዋቅርን መቀላቀላቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከዚያ አስቀድመው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በውኃ ምኅንድስና ሙያቸው…
Read More
ኩዌት ኢትዮጵያዊን ሰራተኞችን ለመቅጠር ተስማማች

ኩዌት ኢትዮጵያዊን ሰራተኞችን ለመቅጠር ተስማማች

ኢትዮጵያና ኩዌት የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ኢትዮጵያና ኩዌት በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እና በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢ ፈርመውታል። በመግባቢያ ስምምነቱ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሠለሞን ሶካ እና ዳንኤል ተሬሳ፣ በኩዌት የኢትዮጵያ አምባሳደር ሰኢድ ሙሁመድ፣ በኢትዮጵያ የኩዌት አምባሳደር ናይፍ ሃኘስ አል ኦይታይቢን ጨምሮ የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ስምምነቱ ወደ ኩዌት የሥራ ስምሪት የሚያደርጉ ኢትዮጵያውያን መብትና ጥቅማቸው ተጠብቆ ህጋዊ የስራ ዕድል የሚያገኙበትን የትብብር ሁኔታ እንደሚፈጥር ተገልጿል። በነዳጅ የበለጸገችው የመካከለኛው ምስራቅ ሀገር ኩዌት የሦስት ወራት አስገዳጅ ስልጠና የወስዱ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን…
Read More
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባኤ በመንግስት ጫና እየተደረገበት እንደሆነ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባኤ በመንግስት ጫና እየተደረገበት እንደሆነ ገለጸ

የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ላይ የሚደረገው ወከባ እና እስር እንዲቆም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ጠይቋል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) መንግስት ከፍተኛ ጥቃትና ጫና እየፈጸመበት እንደሆነ ባወጣው መግለጫ ገልጿል፡፡ ኢሰመጎ በመግለጫው በመንግስት እየደረሰበት ያለው ጥቃት እና ጫና አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን በመግለጫው ላይ አሳውቋል። ጉባኤው በተለያዩ ጊዜ ተፈጽመውብኛል ያላቸው ጥቃቶች እና ከፍተኛ ጫናዎች በመግለጫው ላይ የዘረዘረ ሲሆን በተቋሙ አመራር ላይ በመንግስት የደህንነት ሰዎች የሚፈጸም ክትትል ፣ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እየጨመረ መምጣታቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ክትትል ስራችሁን ካላቆማችሁ ፤ መንግሥትን በሰብዓዊ መብት ጥሰት መወንጀል ካላቆማችሁ  ' ዋጋ ትከፍላላችሁ ' የሚል ዛቻ እየደረሰበት መሆኑን ገልጿል፡፡ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የምርመራ ስራ በሚሰሩ…
Read More
የሶስት ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች ከስልጣን ተነሱ

የሶስት ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች ከስልጣን ተነሱ

ትምህርት ሚኒስቴር ከገንዘብ ብክነት ጋር በተያያዘ የሶስት ዩንቨርሲቲዎችን ፕሬዝዳንት ከሀላፊነት አንስቷል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የበጀትና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የገንዘብ ሚኒስቴርን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት እንደተገለፀው ዩንቨርሲቲዎች የበጀት ብክነት ፈጽመዋል ተብሏል። የወላይታ ሶዶ፣ የጋምቤላ እና ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲፕሬዝዳንቶች በኦዲት ግኝት ከኃላፊነታቸው እንደተነሱ ትምህርት ሚኒስቴር ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር ባደረገው የስራ ግምገማ ወቅት አስታውቋል፡፡ለአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ እና ሌሎች አራት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ከባድ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በተሠራው የተቋማት ኦዲት ሪፖርት የ2014 በጀት ዓመት ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት ከተሰጣቸው 24 መሥሪያ ቤቶች ውስጥ 13 ተቋማት ላይ አስተደደራዊ ዕርምጃ መወሰዱን ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ…
Read More
በአማራ ክልል ጎጃም ሰከላ 40 ንጹሃን ነዋሪዎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ጎጃም ሰከላ 40 ንጹሃን ነዋሪዎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ከግንቦት 5 እስከ 7 ቀን 2016 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ 40 ሰዎች ተገድለዋል ተብሏል፡፡ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ንጹሃኑን የገደሉት ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ የነበሩ እና የሰርግ ስነስርዓትን ታድመው ሲመለሱ እንደሆነ አሻም ቲቪ ዘግቧል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የተጎጂ ቤተሰቦች እንዳሉት በአካባቢው ከዚህ ቀደም ብሎ ግንቦት 4 በፋኖ ሀይሎች እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል ውጊያ እንደነበር ተናግረዋል። የአካባቢው ነዋሪዎችም በስጋት ምክንያት አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ባህርዳር እና ወደ ሌሎች ገጠራማ አካባቢዎች መሰደዳቸውን ተናግረዋል። የምዕራብ ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ አቶ እድሜአለም አንተነህ በበኩላቸው በአካባቢው ውጊያ እንደነበር ገልፀው ነገርግን አንድም ንፁሃን አልተገደለም ማለታቸውን በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት በአማራ…
Read More
ዘጠኝ ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ህጻናት ከትምህርት ገባታ ውጭ መሆናቸው ተገለጸ

ዘጠኝ ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ህጻናት ከትምህርት ገባታ ውጭ መሆናቸው ተገለጸ

የተባበሩት መንግስታት የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) ባወጣው ሪፖርት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 85 ሚሊየን ህጻናት በትምህርት ገበታ ላይ አይገኙም ብሏል። የሀገሪቱ የትምህርት ሁኔታ አሁንም በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ይገኛል ያለው ዩኒሴፍ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በሀገሪቱ በበርካታ ቦታዎች እየተባባሰ የመጣው ግጭት ነው ሲል ጠቁሟል። በተያዘው የፈረንጆቹ አመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት (ጥር፣ የካቲትና መጋቢት) በሀገሪቱ የተዘጉ ትምህርት ቤቶች ቁጥር በ18 በመቶ ጨምሯል ያለው ዩኒሴፍ ጉዳት የደረሰባቸው የትምህርት ቤቶችን ቁጥር በ5 ነጥብ 5 በመቶ መጨመሩንም ጠቁሟል። በሀገሪቱ 6 ሺ 770 ትምህርት ቤቶች ጉዳት ሲደርስባቸው 6 ሺ 410 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ተዘግተዋል ሲል በየሶስት ወሩ በትምህር ዙሪያ በሚያሳትመው ኒውስሌተር ላይ ባሰፈረው ሪፖርት አስታውቋል። በትምህርት ገበታ ላይ…
Read More