ኢኮኖሚ

የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እንደሚችል አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እንደሚችል አስጠነቀቀ

የአፍሪካ ልማት ባንክ ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ ያሉ ሁለት የባንኩ ሰራተኞች በኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች ድብደባ፣ እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር። ባንኩ እንዳለው ሁለት ሰራተኞቹ የቬና የዲልሎማሲ ጥበቃ ስምምነትን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ቢሮ አስተናጋጅ ሀገራት ስምምነትን የጣሰ ክስተት በኢትዮጵያ መፈጸሙንም ገልጿል። የተፈጠረውን ክስተት ለኢትዮጵያ መንግሥት በይፋ ማመልከቱን የሚገልጸው የአፍሪካ ልማት ባንክ ጉዳዩ መፈጸም እንደሌለበት፣ ህግ መጣሱን እና ጉዳዩ ተመርምሮ እርምጃ እንደሚወሰድ በኢትዮጵያ በኩል ቃል ተገብቶልኛል ሲልም በወቅቱ አስታውቆ ነበር፡፡ ባንኩ አሁን ላይ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል በገባው መሰረት በአጥፊዎች ላይ እርምጃ እንዳልወሰደ እና ጉዳዩን ስለመመርመሩ መረጃ እንዳልሰጠው ገልጿል፡፡ ይህን ተከትሎም ባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮውን ሊዘጋ እና…
Read More
ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በማካሄድ ላይ ላለችው የኢኮኖሚ ሪፎርም እና ችግር ላይ የሚገኘውን የፋይናንስ ሁኔታዋን ለመቅረፍ ያግዛት ዘንድ ከአለም አቀፉ ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። በሀገሪቱ የሚታየውን አመታዊ የበጀት ጉድለቷን ለሞሙላት ያግዛት ዘንድ በልዩ ሁኔታ ከአይኤም ኤፍ ብድር መጠየቋን ዘገባው አመላክቷል። የመንግሥት ባለስለጣናት  ባለፈው ሳምንት ከአለም አቀፍ ቦንድ ገዢዎች ጋር በነበራቸው ስብሰባ በቀጣዩ የፈረንጆች አመት 2024 መጀመሪያ ሶስት ወራት ከአይ ኤም ኤፍ ጋር የብድር ስምምነት ላይ እደርሳለን ብለው እንድደሚያምኑ ተናግረዋል። ሀገሪቱ ያለት የገቢ ንግድ ማስኬጃ የውጭ ምንዛሬ መጠን ክምችት ዜሮ ነጥብ ሁለት በመቶ ብቻ እንደሆነ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ኢትዮጵያ የገጠማትን የበጀት ጉድለት ለመሙላት…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ብራዛቪል በረራ የጀመረበትን 40ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ብራዛቪል በረራ የጀመረበትን 40ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኮንጎ ዋና ከተማ ብራዛቪል የቀጥታ በረራ የጀመረበትን ዓመት አክብሯል፡፡ በአፍሪካ ከተመሰረተ ረጅም ዓመት ያስቆጠረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈረንጆቹ 1983 ላይ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ ወደ ብራዛቪል አድርጎ ነበር፡፡ አሁን ላይ አየር መንገዱ በሳምንት 10 በረራዎችን ከአዲስ አበባ-ብራዛቪል የደርሶ መልስ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ከ63 በላይ ከተሞች በመብረር ላይ ሲሆን ይህም ከየትኛውም የዓለማችን አየር መንገዶች በላይ በአፍሪካ ሰማይ ላይ የሚበር አየር መንገድ አድርጎታል፡፡ በታህሳስ 1945 የተመሰረተው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመሪያ በረራውን ወደ ግብጽ ካይሮ አድርጓል፡፡ የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዱባዩ ኤርሾው ላይ ተገኝተው እንዳሉት አየር መንገዱ ከቦይንግ እና ኤርባስ 78 አውሮፕላኖችን ለመግዛት…
Read More
በቢሾፍቱ ከተማ በአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የኤርፖርት ከተማ ሊገነባ ነው

በቢሾፍቱ ከተማ በአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የኤርፖርት ከተማ ሊገነባ ነው

የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አዲሱን 5 ቢሊየን ዶላር ሚያወጣ ‘የኢትዮጵያ አየር  መንገድ ከተማ’ ግንባታ በአራት ዓመታት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሠራ መሆኑን ገለጸ፡፡ አየር መንገዱ “ኤርፖርት ሲቲ” ብሎ የሚጠራውን ግንባታ ለመጀመር ከጫፍ የደረሰው እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለማርካት መሆኑን የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ የንግድ ሥራ ዘርፍ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ለማ ያደቻ ተናግረዋል፡፡ የ ‘ዓየር መንገድ ከተማው’ ካልተገነባ ዓየር መንገዱ በዘርፉ እያስመዘገበ ካለው ፈጣን ዕድገት አንጻር እንደሚፈተን ከግምት ውስጥ በማስገባት ፕሮጀክቱ መታቀዱን አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 5 ቢሊየን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፥ በዓመት 100 ሚሊየን መንገደኞችን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል። አሁን ላይ ዓየር መንገዱ በኦሮሚያ ክልል ከቢሾፍቱ ከተማ ጥቂት ወጣ ብሎ በሚገኝ ሥፍራ የመጀመሪያውን የ ‘ዓየር መንገድ…
Read More
ብሔራዊ ሎተሪ የ8 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እድለኛ እንደጠፋበት ገለጸ

ብሔራዊ ሎተሪ የ8 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እድለኛ እንደጠፋበት ገለጸ

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር በየጊዜው ለሽፓጭ ከሚያውላቸው የእድል ሎተሪዎች መካከል የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አንዱ ነው። 20 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ይህ እጣ ባሳለፍነው ጷግሜ 2015 ዓም እጣው የወጣ ሲሆን 1820259 ደግሞ የመጀመሪያ እድለኛ ቁጥር እንደሆነ በወቅቱ ተገልጿል። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር ኮሙንኬሽን ዳይሬክተር አቶ ቴድሮስ ንዋይ ለዓልዐይን እንዳሉት "ባሳለፍነው ጷግሜ ላይ ከወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ከሶስት እጣ አሸናፊ በስተቀር የሁለት እጣ አሸናፊዎች እስካሁን አልመጡም" ብለዋል። ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድሩ የሁለት እጣ እድለኞች ማለትም የስምንት ሚሊዮን ብር አሸናፊዎች እስከ ቀጣዩ የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ካልመጡ ገንዘቡ ለመንግሥት ገቢ ይሆናልም ብለዋል። 20 ሚሊዮን ብር ከሚያሸልመው እጣ ቁጥር ውስጥ እስካሁን በመተሀራ ከተማ በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ በወዛደርነት…
Read More
ኤምፔሳ ሳፋሪኮም ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቼን ልሸልም ነው አለ

ኤምፔሳ ሳፋሪኮም ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቼን ልሸልም ነው አለ

ኤምፔሳ ሳፋሪኮም አዲስ ተጠቃሚ እና ግብይታቸውን በM-PESA የሚያካሒዱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን፣ ወኪሎችን እና ነጋዴዎችን የሚሸልምበት ከታህሳስ 1 ቀን እስከ መጋቢት 2 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የ9ዐ ቀናት የሽልማት መርኃ ግብር ትናንት ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ በይፋ አስጀምሯል። ተረክ በኤምፔሳ ደንበኞች እና ድርጅቶች የኤምፔሳ አዲስ ተጠቃሚ በመሆናቸው እና ግብይታቸውን በኤምፔሳ በማካሔዳቸው የእጣ ቁጥሮችን በመሸለም ስለ ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎቱ የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠር እና አጠቃቀሙን ለማጎልበት ያለመ መርኃ ግብር ነው። በእጣዎቹ የሚገኙ ሽልማቶች አራት መኪኖች፣ 12 ባጃጆች፣ 2160 የስልክ ቀፎዎች እና የአየር ሰዓት ስጦታዎች ይሆናሉ፡፡ እያንዳንዳቸው ደንበኞች በአንድ ቀን የሚደርሳቸው ከፍተኛ የእጣ ብዛት 10 ሲሆን ይህም በየእለቱ፣ በሁለት…
Read More
ኢትዮጵያ ብድራቸዉን መክፈል ከማይችሉ ሀገራት ተርታ ተመደበች

ኢትዮጵያ ብድራቸዉን መክፈል ከማይችሉ ሀገራት ተርታ ተመደበች

መንግስት ከወሰደዉ የረጅም ጊዜ ብድር እና ወለድ አከፋፈል ዙሪያ ከአበዳሪዎች ጋር በዚህ ሳምንት ተጨማሪ ውይይት ለማድረግ ማቀዱ ተገልጿል የኢትዮጵያ መንግስት እ.ኤ.አ በ2014 በዩሮ ቦንድ ከተበደረዉ የ1 ቢሊዮን ዩሮ እና ወለዱን 33 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ የመክፈል አቅም ስለመኖሩ አበዳሪዎች ከጥርጣሬ ዉስጥ መገባታቸዉን ብሉምበርግ አስነብቧል። በዘገባዉ ኢትዮጵያ ዛምቢያንና ጋናን በመከተል በአፍሪካ የከሰሩ ሀገራት ተርታን ልትቀላቀል ከጫፍ የደረሰች መሆኑን ዘገባዉ ጠቅሷል። በተያዘዉ ሳምንት ሐሙስ መንግስት ከአበዳሪ አካላት ጋር ዉይይት የማድረግ እቅድ ስለመኖሩ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ መንግስት ከአንዳንድ አበዳሪ አካላት ጋር ባሳለፍነዉ ሳምንት የተገደበ ዉይይት አድርጎ አበዳሪዎች ኢትዮጵያ ያለባትን የ33 ሚሊዮን ዶላር የወለድ እዳ የመክፈል አቅም እንደሌላት ተገንዝበዋል ብሏል። ለዚህም ኢትዮጵያ የዉጭ ምንዛሬ መጠባበቂያ…
Read More
አማራ ባንክ ፕሬዝዳንቱን ከሀላፊነት አነሳ

አማራ ባንክ ፕሬዝዳንቱን ከሀላፊነት አነሳ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኄኖክ ከበደ ከሓላፊነታቸው ተነሱ የአማራ ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳንቱ አቶ ሔኖክ ከበደ ባንኩን ለ460 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ዳርገዋል በሚል ከሀላፊነት አንስቷል፡፡ ባንኩ ከዋና ሥራ አስፈጻሚው በተጨማሪም የኮርፖሬት አገልግሎት ዋና መኰንኑን አቶ ክንዴ አበበን፣ የአፈጻጸም ድክመት አሳይተዋል በሚል በባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር  መላኩ ፈንታ ፊርማ ከሓላፊነታቸው አንሥቷል። የባንኩ ቦርድ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ ኹለቱም ከፍተኛ ሓላፊዎች፣ ከተሾሙበት ዕለት ጀምሮ፣ በየጊዜው በሚሳዩት የሥራ አፈጻጸም ድክመት፣ የባንኩን ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ቁልፍ የአፈጻጸም መመዘኛዎችን ማሳካት አልቻሉም ተብሏል፡፡ ባንኩ በ2014/15 ዓ.ም. ከ306 ሚሊዮን ብር በላይ ትርፍ ለማስመዝገብ ዐቅዶ የነበረ ቢኾንም፣ ብር 460,286,000 ኪሳራ አስመዝግቧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በሌላቸው ሥልጣን ባሳለፉት አስተዳደራዊ…
Read More
ኢትዮጵያ በ50 ሚሊዮን ዶላር የትራክተር ፋብሪካ ልትገነባ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በ50 ሚሊዮን ዶላር የትራክተር ፋብሪካ ልትገነባ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ በሞጆ ከተማ በ50 ሚሊዮን ዶላር የትራክተር ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አምባሳደር ሱለይማን ደደፎ ተናግረዋል። ፋብሪካው ትራክተር የሚገጣጥም ሳይሆን ትራክተሩን ለማምረት የሚያስችሉ ዕቃዎችን የሚያመርት እራሱን የቻለ ፋብሪካ ይሆናልም ብለዋል። ተገዝተው በሚመጡ ትራክተሮች ብቻ የኢትዮጵያን ግብርና ማዘመን አይቻልም ያሉት አምባሳደር ሱሌይማን፤ ኢትዮጵያ የራሷን “ብራንድ” መትከል ስለሚገባት በሚሊዮን የሚቆጠር ትራክተር የሚያመርት ፋብሪካ መገንባት አለበት ብለን ወደ ተግባር በመግባት ላይ እንገኛለን ብለዋል። ፋብሪካው የትራክተር ሞተር ጭምር የሚያመርት ስለመሆኑ የጠቀሱ ሲሆን፤ ባሉን ፋብሪካዎችም የመኪና የውስጥ ክፍል “ሻንሲ” የመሥራት አቅም እያዳበርን በመሆኑ፤ ሞተር ማምረት ከቻልን መኪና የማምረት አቅም ላይ እንደሚደረስ ተናግረዋል፡፡ አሁን በመላ ሀገሪቱ በተጨባጭ ያሏት የትራክተሮች ቁጥር ከ100 ሺ…
Read More
ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ

ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ

የዓለማችን ስመ ገናናው የአቪዬሽን ተቋም ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ዳይሬክተር አድርጎ መሾሙን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው እንዳስታወቀው በፈረንሳይ የቀድሞ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን የአፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አድርጎ እንደሾመ አስታውቋል፡፡ ቦይንግ አምባሳደር ሔኖክን የሾመው ኩባንያው ከአፍሪካ ጋር የሚኖረውን የንግድ እና ሌሎች ግንኙነት እንዲያሳልጡለት መሆኑን ገልጿል፡፡ አምባሳደር ሔኖክ አዲስ አበባ ሆነው ስራቸውን ያከናውናሉ የተባለ ሲሆን በቦይንግ የመካከለኛው ምስራቅ፣ ቱርክ እና አፍሪካ ፕሬዝዳንት ለሆኑት ኩልጂት ጋታ አውራ ጋር ይሰራሉ ተብሏል፡፡ ቦይንግ የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ እንደሚከፍት የገለጸ ሲሆን አምባሳደር ሔኖክ ደግሞ የኩባንያውን የአፍሪካ ስራዎች እንደሚመሩ አስታውቋል፡፡ አምባሳደር ሔኖክ በአቪዬሽን ንግድ ዘርፍ እና መንግስታዊ ግንኙነቶችን በመምራት ጥሩ ልምድ እንዳለቸው የገለጸው ቦይንግ በአፍሪካ…
Read More