ኢኮኖሚ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በመከታተል እና ሪፖርቶችን በማውጣት የሚታወቀው ኔት ብሎክስ የ2023 ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ ተቋም ሪፖርት መሰረት ኢትዮጵያ ከኢንተርኔት በመዝጋት ገቢ ካጡ ሀገራት መካከል ከሩሲያ በመቀጠል ከፍተኛ ገቢ ያጣች ሀገር ተብላለች፡፡ ሩሲያ 113 ሚሊዮን ዜጎቿን ከኢንተርኔት ውጪ በማድረጓ አራት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ስታጣ ኢትዮጵያ ደግሞ 30 ሚሊዮን ገደማ ዜጎች ከኢንተርኔት አገልግሎት ውጪ ተደርገዋል፡፡ ሆን ተብሎ በመንግስት እንደተወሰደ የተገለጸው ይህ ኢንተርኔት ማቋረጥ ኢትዮጵያ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አሳጥቷታል ተብሏል፡፡ ሀገራት ኢንተርኔት አገልግሎቶችን የሚያቋርጡት በሶስት ምክንያት ነው የተባለ ሲሆን ተቃውሞዎችን ለማፈን፣ የሀሳብ ነጻነትን ለመገደብ እና የምርጫ ስራዎች እንዳይታወኩ በሚል እንደሆነም ተገልጿል፡፡ 25 የዓለማችን ሀገራት ኢንተርኔት አቋርጠዋል የተባለ ሲሆን…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መስጠት አቆመ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መስጠት አቆመ

በኢትዮጵያ ካሉ የንግድ ባንኮች መካከል አንጋፋ እና ሀብታም የሆነው የንግድ ባንክ ብድር መስጠቱን አቁሟል፡፡ ንግድ ባንኩ ብድር ለማግኘት የተለያዩ ሂደቶችን አልፈው ፤ ብድሩ ተፈቅዶላቸው የመልቀቅ ሂደት ላይ ያሉትም እንዲቆም ማዘዙ ተገልጿል፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የባንኩ ደንበኛ ለኢትዮ ነጋሪ እንዳሉት የንግድ ባንክ ብድር ተፈቅዶልኝ ገንዘቡን ለመረከብ በመጠባበቅ ላይ እያለሁ ብድሩ ለጊዜው እንዲቆም መወሰኑ ተነግሮኛል ብለዋል፡፡ ሌላኛው የባንኩ ደንበኛ በበኩሉ ሶስት ሚሊዮን ብር ብድር ለመውሰድ አስፈላጊውን መስፈርቶች ሁሉ አሟልቼ ብሩ እንዲለቀቅልኝ እየተጠባበቅሁ እያለ የቅርንጫፉ ስራ አስኪጅ ደውለው ብድሩ መታገዱን ነገሩኝ ሲልም ነግሮናል፡፡   ባንኩ ብድር እንዲቆም ትእዛዝ ያስተላለፈው ከመጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ነውም ተብሏል፡፡ ንግድ ባንኩ በጊዜያዊነት ብድር መልቀቅ…
Read More
ኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ከግብር ነጻ እድል ፈቀደች

ኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታት ከግብር ነጻ እድል ፈቀደች

የኢትዮጵያ ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ለጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ወይም ስታርት አፕ የተለያዩ ማበረታቻዎችን መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ለስራ ፈጣሪዎች ከተደረጉት ማሻሻያዎች መካከል ከግብር ነጻ እድል፣ ከውጭ ንግዶች የሚያገኟቸውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ሙሉ ለሙሉ እንዲወስዱ፣ ንግድ ፈቃድ ለማውጣት የግድ ቢሮ ያስፈልግ የነበረውን ማንሳት፣ አዲ ሀሳብ ላላቸው ብድር ማመቻቸት እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ይህ አውደ ርዕይ ለ20 ቀናት ይቆያል የተባለ ሲሆን ጎብኚዎች ወደ ሳይንስ ሙዚየም በማቅናት መግባት እና መጎብኘት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡ ከተደረጉ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

ኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ የ1 ነጥብ 72 ቢሊዮን ዶላር ወይም የ97 ቢሊዮን ብር እርዳታ እና በድር ስምምነት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ተወካይ የሆኑት ኦስማን ዲዮን ተፈራርመዋል ተብሏል፡፡ ከዓለም ባንክ ከተገኘው የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ 850 ሚሊዮን ዶላር ያህሉ በእርዳታ ለኢትዮጵያ የተለያዩ ስራዎችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ቀሪው ገንዘብ ደግሞ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት እና ለማከናወን በሚል በብድር መልኩ ከባንኩ እንደተሰጠ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ በእርዳታ ከተሰጠው ገንዘብ ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላሩ ለገጠር አካባቢዎች የምግብ ዋስትና፣ የአየር ንብረት ለውጥ ስራዎችን ለመደገፍ፣ 82 ዶላሩ ደግሞ በከተማ አካባቢዎች ምግብ ዋስትና ስራዎችን ለማረጋገጥ…
Read More
የኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ ዉይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ ዉይይት ያለ ስምምነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት እና ሀገራት ጋር እያደረገችው ያለው ውይይት አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋሙ አይኤምኤፍ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይቶችን ከሚያደርጉ አበዳሪ ተቋማት መካከል ዋነኛው ሲሆን ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ቆይታ አድርጎ መመለሱ ተገልጿል፡፡ አይኤምኤፍ በድረገጹ ባወጣው መረጃ በኢትዮጵያ መንግስት ጥያቄ መሰረት ከመጋቢት 10 እስከ 24 ቀን 2016 ዓም ድረስ በአዲስ አበባ ቆይታ አድርጎ ተመልሷል፡፡ ኢትዮጵያ ልታካሂደው ባሰበችው የኢኮኖሚ ሪፎርም ላይ አይኤምኤፍ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥያቄ እንዳቀረበች የገለጸው ይሄው ተቋም በአልቫሮ ፒሪስ የተመራ የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ቡድን ወደ አዲ አበባ መምጣቱን አስታውቋል፡፡ ለ15 ቀናት በዘለቀው በዚህ የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ ባለሙያዎች እና ባለስልጣናት መካከል የተደረገው ውይይት ገንቢ እንደነበርም ተገልጿል፡፡…
Read More
መንግስት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን መቆጣጠር የሚያስችለውን ህግ አወጣ

መንግስት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን መቆጣጠር የሚያስችለውን ህግ አወጣ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን አጽድቋል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ አጽድቋል። በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ተስፋዬ በልጂጌ ለምክር ቤቱ አባላት በሰጡት ማብራሪያ፤ መንገግስት የዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት የሆነውን የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ለማሻሻል የተለያዩ ጥረቶች እያደረገ ቢሆንም፤ ከመኖሪያ ቤት ፍላጎት ጋር ሊጣጣም አልቻለም ብለዋል። አቶ ተስፋዬ አክለውም ፤ በኢትዮጵያ የተጋነኑ እና ከተከራዮች የመክፈል አቅም በላይ የሆነ የቤት ኪራይ ጭማሪዎች በከተሞች እንዳሉ ተናገረዋል፡፡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ በተለይ በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ እና ዜጎችም ተረጋግተው ኑሯቸውን…
Read More
ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ እንደምታነሳ ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ እንደምታነሳ ገለጸች

ኢትዮጵያ የየነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ሀገራት በመግዛት የምትሸፍን ሲሆን የትራንስፖርት ዋጋ እንዳያንር በሚል የነዳጅ ድጎማ ስታደርግ ቆይታለች፡፡ የመንግስት ወጪ በመጨመሩ እና የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ እና ለማቆም እንደወሰነች የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባሳለፍነው ዓመት ይፋ አድርጓል፡፡ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለማይሰጡ ድርጅቶች የነዳጅ ድጎማው ከቆመ አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን አሁን ደግሞ የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችም የነዳጅ ድጎማ እንደማያገኙ ተገልጿል፡፡ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ድጎማ ሲደረግላቸው የነበሩ የሚኒባስ ተሽከርካሪዎች ከመጋቢት 30 ቀን  2016 ዓ.ም ጀምሮ ድጎማው እንደሚቋረጥ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል። መንግሥት ለረጅም ጊዜ ለነዳጅ ምርቶች ከፍተኛ መጠን የለው ድጎማን ሲያደርግ መቆየቱን በመግለጽ ይህንን ለማስቀረት በሂደት የነዳጅ ምርቶች…
Read More
የአዲስ አበባ እምብርት ከምትባለው ፒያሳ 11 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን ከንቲባ አዳነች ተናገሩ

የአዲስ አበባ እምብርት ከምትባለው ፒያሳ 11 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን ከንቲባ አዳነች ተናገሩ

በአዲስ አበባ ከፒያሳ እና አካባቢው ከሳምንታት በፊት በተጀመረው የከተማ ማስዋብ ግንባታ ምክንያት 11 ሺህ ሰዎች መነሳታቸውን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል። ከንቲባዋ በሁሉም የመንግስት ሚዲያዎች በተላለፈ ንግግራቸው ላይ እንዳሉት “በድምሩ ወደ 11 ሺህ ሰው ይሆናል ከዚያ አካባቢ ወደተሻለ ቦታ የወሰድነው” ብለዋል። ነዋሪዎቹ መኖሪያ ቤታቸው የፈረሰው በፒያሳ አካባቢ ካሉት ራስ መኮንን ድልድይ፣ ማህሙድ ሙዚቃ ቤት፣ የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ፣ አራት ኪሎ የሚገኘው አብርሆት ቤተ መጽሐፍት፣ ቴዎድሮስ አደባባይ እስከ ቸርችል ጎዳና ድረስ በሚያካልለው “የኮሪደር ልማት” ምክንያት የተነሱ ናቸው። ይህ የኮሪደር ልማት ከፒያሳ እስከ አራት ኪሎ ባለው አካባቢ የሚገኝ ሲሆን፣ 8.1 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍንም ከንቲባዋ ገልጸዋል። አዳነች በዚህ ሪፖርት ላይ ከተነሺዎቹ…
Read More
ኢትዮጵያ ከማዕድን ንግድ ከ252 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘሁ አለች

ኢትዮጵያ ከማዕድን ንግድ ከ252 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘሁ አለች

በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ስምንት ወራት ከማዕድን ዘርፍ 252 ነጥብ 15 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል። የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማትዮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳሉት፤ በ2016 በጀት ዓመት የተለያዩ ዓይነት ማዕድናት ወደ ውጭ ገበያ በመላክ 252 ነጥብ 15 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። ባለፉት ስምንት ወራት ከሁለት ሺህ 673 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ፣ 66 ቶን በላይ ታንታለም እና ከ11 ሺህ 176 ቶን በላይ ሉቲየም ኦር ለውጭ ገበያ መቅረባቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም ከ99 ሺህ 021 በላይ ቶን የጌጣጌጥ እንዲሁም 29 ሺህ 281 ቶን በላይ የኢንዱስትሪ ማዕድናት ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉን አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል። የተገኘው ገቢ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት…
Read More
ንግድ ባንክ ከተወሰደበት ጠቅላላ ገንዘብ ውስጥ 372 ሚሊዮን ብር ማስመለሱን አስታወቀ

ንግድ ባንክ ከተወሰደበት ጠቅላላ ገንዘብ ውስጥ 372 ሚሊዮን ብር ማስመለሱን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሁለት ሳምንት በፊት ያጋጠመውን የሲስተም ችግር አስመልክቶ እያደረገ ያለውን ስራ የደረሰበት ደረጃ ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በሰጡት መግለጫ፤ ችግሩ የት ጋር ነው ያጠመው የሚለው ላይ በባለሙያ ጥናት እየተደረገ ነው ገና አላለቀም ብለዋል። በእለቱ ከተፈጠረው የሲስተም ችግር ጋር ተያይዞ በተደረጉ ግብይች እና የገንዘብ ዝውወሮች ዙሪያም ማብራሪያ ሰጥተዋል። በእለቱ ሊጠፋ የነበረ ወይም አንድ ሰው ገንዘብ ከአካውንቱ ገንዘብ ካስተላለፈ በኋላ ለተላከለትም ሰው ደርሶ ገንዘቡ ለላኪውም ተመለሶ የተተካ ወይም ሪቨርስ ያደረገ 801 ሚሊየን 417 ሺህ 800 ብር  ነበር ብለዋል። በእለቱ አጋጥሞ በነበረ የሲስተም ችግር በነበረበት መስመር ላይ 25 ሺህ 761 ደንበኞች ገብይት ፈጽመዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤…
Read More