Blog

42 ማርኬትስ  ግሩፕ  አስር ሚሊየን ዶላር  ድጋፍ ማግኘቱን ገለፀ

42 ማርኬትስ  ግሩፕ  አስር ሚሊየን ዶላር  ድጋፍ ማግኘቱን ገለፀ

ድርጅቱ ድጋፉን ያገኘው  በግል ባለሀብት ከሚንቀሳቀሰውና  በደቡብ ሰሀራ ሀገራት   በቴክኖሎጂ ላይ ከሚሰራው  ከኮንቨርጀንስ  ፓርተንርስ እና  ከ14  ዓለም ዓቀፍ   የገንዘብ ልማት  ላይ ከሚሰሩ ታዋቂ  የገንዘብ  ተቋማት ነው። በቅርቡ  በዲጂታል   የመሰረተ ልማት ላይ ስራዎች የገንዘብ አቅርቦት ፕሮጅክቱን በ 296 ሚልየን የአሜሪካ ዶላር ያጠናቀቀው  42 ማርኬትስ ግሩፕ ለተጠቃሚዎች ወይም ለንግድ ድርጅቶች የገንዘብ ልውውጥ  ላይ ከሚሰራው ፊንቴክ ቡድን ወስጥ አንዱ  ቡድን ነው። የ 42 ማርኬትስ ግሩፕ  ስራ አስኪያጅ  አንድሪስ ብሪንክ እንዳሉት  "የተገኘው ገንዘብ ድጋፍ  የዲጂታል ገንዘብ መሰረተልማቱ   ትክክለኛ መተማመኛ እንዲያገኝ ከማድረጉ ባሻገር    ለቀዘቀዘውም  ሆነ እያደገ ለሚመጣ  ገበያ  በጎ የኢንቨስትመንት  ተፅዕኖ እንዲኖረው ያደርጋል" ብለዋል። ከ42 ማርኬትስ ግሩፕ   የበሰሉ ስራዎች ከሚሰሩት  ድርጅቶች መካከል የካፒታል እና  ገበያ አገልግሎቶች …
Read More
በሚዛን አማን ሁለት ህጻናት በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

በሚዛን አማን ሁለት ህጻናት በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

በኢትዮጵያ ሁለት ህጻናት በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው አለፈበመብረቅ አደጋ የአምስት እና የሰባት አመት እድሜ ያላቸዉ የሁለት ታዳጊ ህፃናት ህይወት ማለፉ ተገልጿል። በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በመብረቅ አደጋ የሁለት ታዳጊ ህፃናት ህይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡ በከተማው አዲስ ከተማ ቀበሌ ልዩ ስሙ ብርሃን አዲስ ከተማ ሠፈር ከቀኑ 8፡30 የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው መብረቅ የሁለት ህፃናት ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል። አደጋው የደረሰው ሶስት ህጻናት ውሃ ለመቅዳት ወንዝ በሄዱበት ወቅት ዝናብ በመዝነቡ ለመጠለል ዛፍ ስር በሚገኝ ድንጋይ ላይ በተቀመጡበት ወቅት ነው። በዚህ የመብረቅ አደጋ ምክንያትም የሁለቱ ህፃናት ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው የሚያልፉ ዜጎች…
Read More
የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የዘጠኝ ወራት የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ። የንግድ እና ቀጠናዊ ውህደት ሚንስቴር እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር። ይሁንና የተገኘው ገቢ ግን በአንድ ቢሊዮን ዶላር ቀንሶ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ተብሏል። ለገቢው መቀነስ የጸጥታ ችግሮች፣ ህገወጥ ንግድ፣ የዓለም ንግድ መቀዛቀዝ እና የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ከተገኘው ገቢ ውስጥም ግብርና የ77 በመቶ ድርሻ ሲያዝ ቀሪው ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ እና ኤሌክትሪክ ሽያጭ እንደሆኑ ሚንስቴሩ ገልጿል ባለፉት ሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ የቆየችው ኢትዮጵያ የወጪ ንግዷ ተዳክሞ የቆየ ሲሆን በአሜሪካ የተጣለባት ማዕቀብ፣ ህገወጥ የማዕድን ገበያ መስፋፋት ለወጪ ንግዱ ዋነኛ ችግሮች…
Read More
ኢትዮጵያ ለሱዳን 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደምትልክ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሱዳን 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደምትልክ ገለጸች

ኢትዮጵያ 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ ለሱዳን ለመላክ መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ በ”ኢትዮጵያ ኤይድ” በኩል የሚቀርበው ድጋፍ በርካታ መድሃኒቶችንም እንደሚያካትት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል ። ለሱዳን ህዝብ በአሁኑ ወቅት የሚያስፈልገውን ድጋፍ ከማቅረብ ባሻገር ተፋላሚዎቹን ወገኖች ለመሸምገልም ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳላት አንስተዋል። ለሱዳን ጦር መሪ ጀነራል አልቡርሃን እና ለፈጥኖ ደራሽ ሃይል (አርኤስኤፍ) አዛዡ ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎም በድጋሚ ለንግግር ቦታ እንዲሰጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰሜኑ ጦርነት በድርድር እንዲቆም ላደረጉ አካላት እውቅና ሲሰጡ ነው ጥሪውን ያቀረቡት። የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በሽብርተኝነት ከተፈረጀው የኦሮሚያ ነጻ አውጭ ሰራዊት ጋር ድርድር እንደሚደረግ ተናግረዋል ። ድርድሩ በታንዛኒያ የሚካሄድ ሲሆን ኖርዌይ እና ኬንያ አደራዳሪዎች ይሆናሉ ተብሏል።
Read More
ሲፋን ሀሰን የለንደን ሜራቶንን አሸነፈች

ሲፋን ሀሰን የለንደን ሜራቶንን አሸነፈች

የለንደን ማራቶች ከደቂቃዎች በፊት የሁለቱም ጾታ ተዉዳዳሪዎች ፍጻሜውን አግኝቷል። በዚህም ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ እና በዜግነት ሆላንዳዊ የሆነችው ሲፋን ሀሰን አንደኛ ወጥታለች። ለመጀመሪያ ጊዜ በማራቶን ውድድር ላይ የተሳተፈችው ሲፋን ርቀቱን በ2 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ37 ማይክሮ ሰከንድ አጠናቃለች። ኢትዮጵያዊቷ መገርቱ አለሙ ሁለተኛ ጀፕችርችር ፒሬዝ ከኬንያ ሶስተኛ ወጥተዋል። በርቀቱ ተጠብቃ የነበረችው አልማዝ አያና ውድድሯን በሰባተኝነት አጠናቃለች። በወንዶች የማራቶን ውድድር ደግሞ ኬንያዊው ኬልቪን ኪፕቱም በ2 ሰዓት ከአንድ ደቂቃ ከ25 ማክሮ ሰከንድ አንደኛ ሲሆን ሌላኛው ኬንያዊ ጂዎፍሪ ካምዎሮር ሁለተኛ እንዲሁም ኢትዮጵያዊው ታምራት ቶላ ደግሞ ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል። ልኡል ገብረስላሴ እና ሰይፉ ቱራ ደግሞ አራተኛ እና አምስተኛ ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁ የኢትዮጵያ አትሌቶች ናቸው። በውድድሩ ተጠብቀው የነበሩት…
Read More
አሜሪካንን ጨምሮ በርካቶች ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን እያስወጡ ነው

አሜሪካንን ጨምሮ በርካቶች ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን እያስወጡ ነው

አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ዲፕሎማቶቻቸውን ከሱዳን ካርቱም ማስወጣት ጀምረዋል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ በሱዳን ካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶች እና ቤተሰቦቻቸው በዛሬው ዕለት ሀገሪቷን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዲፕሎማቶቹ የአሜሪካ ጦር ባካሄደው የተሳካ ኦፕሬሽን ከሱዳን ካርቱም በሰላም መውጣት ችለዋል ተብሏል። ፕሬዚዳንት ባይደን ዲፕሎማቶችን ለማስወጣት ለተደረገው የተሳካ ስራ ለኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ እና ሳዑዲ ዓረቢያ መንግስታት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አሁን ላይ በሱዳን የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ አገልግሎት መስጠት እንዳቆመ አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ 150 የሚሆኑ የሳዑዲ ዓረቢያ፣ ግብጽ፣ ካናዳ፣ ሕንድ፣ ኩዌት፣ ፓኪስታን እና የቱኒዚያ ዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት አመራሮች በባህር ከሱዳን ሳዑዲ ዓረቢያ መግባታቸው ተገልጿል። ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ብሪታንያ፣ ስፔን እና ሌሎች ሀገራትም በሱዳን ካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶቻቸውን…
Read More
በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ

በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14 ቀን 2014 ዓ.ም:- ሀገራት ዜጎቻቸውን እያስወጡ ያሉት በጋላባት-መተማ በኩል ነው ተብሏል ዜጎችን የማስወጣት ስራው በካርቱም ካለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ጋር በመነጋገር ነው በሱዳ. ያሉ የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ የተለያዩ ሀገራት በሱዳን ያሉ ዜጎቻቸውን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ጀምረዋል። በሱዳን ብሔራዊ ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ መካከል የተጀመረው ጦርነት ስምንተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል። ለኢድ በዓል ተብሎ የሶስት ቀን ተኩስ አቁም ቢደረግም ጦርነቱ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ተብሏል። ይህ በዚህ እንዳለ የተለያዩ ሀገራት በሱዳን የሚገኙ ዜጎቻቸውን ለማስወጣት ትረቶች ላይ ይገኛሉ። ከካርቱም ዜጎቻቸውን በአየር ትራንስፖርት ለማውጣት ያልተሳካላቸው ሀገራት በየብስ ትራንስፖርት በኢትዮጵያ ድንበር በኩል እያስወጡ መሆኑን ሰምተናል። ሀገራቱ…
Read More
አሜሪካ አንድ ዜጋዋ ሱዳን ውስጥ እንደተገደለባት ገልጸች

አሜሪካ አንድ ዜጋዋ ሱዳን ውስጥ እንደተገደለባት ገልጸች

አንድ የአሜሪካ ዜጋ ሱዳን ውስጥ እየተካሄደ ባለው ውጊያ መገደሉ ተሰምቷል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለፎክስ ኒውስ በሰጠው ቃል ፤ በሱዳን አንድ አሜሪካዊ ዜጋ መሞቱን አረጋግጧል። መስሪያ ቤቱ ፤ ከሟች ቤተሰብ ጋር እየተገናኘ መሆኑንና በደረሰባቸው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል። "በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ለቤተሰብ ካለን አክብሮት የተነሳ ምንም የምንጨምረው ነገር የለም " ሲልም ስለ ሟች ዝርዝር መረጃ ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል። በሌላ በኩል ፤ የአሜሪካ መከላከያ ጦር በአፍሪካ ኮማንድ በኩል በሱዳን ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ መሆኑን አሳውቋል። አሜሪካ በሱዳን ያሉ ዜጎቿን ደህንነት ለማረጋገጥ ወደ ጅቡቲ ተጨማሪ ወታደሮችን ለመላክ እያሰበች መሆኗንም አስታውቃለች። የአሜሪካ ጦር ፤ በካርቱም የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲ ሰራተኞችን እና ዜጎችን ለማስወጣት የሚያስችለውን…
Read More
ኢትዮጵያ ጦሯን ወደ ሱዳን አስገብታለች መባሉን አስተባበለች

ኢትዮጵያ ጦሯን ወደ ሱዳን አስገብታለች መባሉን አስተባበለች

በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ባለችው ሱዳን እስካሁን የተገደሉ ዜጎች ቁጥር ከ350 በላይ አሻቅቧል። ይህ በዚህ እንዳለ የኢትዮጵያ ጦር ወደ ሱዳን ግዛት ገብቶ ወረራ ፈጽሟል የሚሉ ዜናዎች በበርካታ የሱዳን ሚዲያዎች ተዘህበዋል። ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ዛሬ ባወጣችው መግለጫ ምንም አይነት ወታደር ወደ ሱዳን ግዛት አለማስገባቷን አስታውቃለች። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ "በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ግጭት መቀስቀስ የሚፈልጉ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በመግለጫቸው አንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ እና ሱዳን ግንኙነትን ለማበላሸት በማሰብ፣ "ኢትዮጵያ ወታደሮቿን ሱዳን ውስጥ አስገብታለች በማለት ሐሰተኛ መረጃ እያሠራጩ ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ውዝግብ ቢኖራቸውም ልዩነታቸው በንግግር ይፈታል ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል። "ኢትዮጵያ አሁን ሱዳን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ለድንበር…
Read More
በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ ከአዲሱ ገበያ ከፍ ብሎ እንጦጦ መስመር ላይ የተገነባው፤ "ስቴይ ኢዚ ፕላስ" ሆቴል ከኹለት ሳምንታት በኋላ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ አቶ አሚር ሰኢድ እንዳሉት ሆቴሉ በጥንዶቹ ዳግማዊ መኮንን እና ህይወት አየለ ባለቤትነት የተገነባ ሲሆን ሆቴሉ ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ፈጅቷል ብለዋል፡፡ በአምስት ዓመት ውስጥ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ታስቦ ግንባታው የተጀመረው ይህ ባለ ስምንት ወለል ህንጻ ኮሮና ቫይራ ተጨምሮበት በስምንት ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ሆቴሉ በባለ አምሰት ኮከብ ደረጃ መገንባቱን የተናገሩት ደግሞ የሆቴሉ ባለቤት እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ወይዘሮ ሂወት አየለ ናቸው፡፡ እንደ ወይዘሮ ሂወት ገለጻ ሆቴሉ በአጠቃላይ 103 ክፍሎች፣ ከ15 እስከ 1 ሺሕ…
Read More