TPLF

ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

ራያ እና ወልቃይት አካባቢ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው አካባቢዎች ምርጫ እንዲካሄው ውስኗል ተብሏል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የካቲት 16፣ 2018 ባወጣው መግለጫ ከዚህ በፊት በትግራይ ክልል ስር ሆነው ምርጫ ሲካሄድባቸው የነበሩ ምርጫ ክልሎች ከክልሉ መንግስት ውጪ ሆነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድባቸው መወሰኑን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሰው ገልጿል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቻ ይካሄድባቸዋል ተብለው በቦርዱ መግለጫ ላይ የተጠቀሱት ምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲረመጽ፣ ኮረምኦፍላ ፣ ጠለምት እና ራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች እንደሆኑም ቦርዱ አስታውቋል፡፡ ቦርዱ አክሎም የክልል ምክር ቤት ምርጫ በአካባቢዎቹ ላይ የተነሳባው የይገባኛል ውዝግብ ጥያቄ በህገ መንግስት ውሳኔ መሰረት ሲፈታ እንደሚካሄድ ቦርዱ አስታውቋል።የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር በበኩሉ…
Read More
የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ

የኤርትራ ጦር ከአማጺ ጋር በመተባበር ወደ ኢትዮጵያ ግዛት መግባቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እንዳስታወቀው ኤርትራ ባለፉት ቀናት አዲስ ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋልል። ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ለኤርትራ አቻቸው ኦስማን ሳሌህ በጻፉት ደብዳቤ የኤርትራ ጦር ከአማጺያን ጋር በመተባበር በሰሜን ምስራቅ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን አስታውቋል። ወደ ኢትዮጵያ የገቡት የኤርትራ ወታደሮችም ከአማጺያን ጋር በመቀናጀት ወታደራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ እንደሆኑም ተገልጿል። በመሆኑም እነዚህ የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያ ባስቸኳይ እንዲወጡም ጠይቋል። የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ በደብዳቤው ላይ ከኤርትራ ጋር የገቡበትን አለመግባባት በዲፕሎማሲ ለመፍታት ዝግጁ እንደሆነም ገልጿል። ሚንስትሩ አክለውም በተለይ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት እና የአሰብ ወደብን ለማግኘት ያቀረበቻቸውን ጥያቄዎች ጨምሮ ሌሎች ፍላጎቶችን ሁለቱን ሀገራት ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ ለመወያየት ዝግጁ እንደሆነችም ተጠቅሷል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው…
Read More
በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ነዋሪዎች ተናገሩ

በትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው ነዋሪዎች ተናገሩ

በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ባለፉት ሶስት ቀናት የተፈጠሩ አለመረጋጋቶች ነዋሪዎችን እንዳስጨነቃቸው ተናግረዋል፡፡ ያነጋገርናቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት የትግራይ ታጣቂዎች ከነ ትጥቃቸው ወደ ከተማዋ በመግባት ሲንቀሳቀሱ የታዩ ሲሆን በተለይም የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አካባቢ ያለው ሁኔታ አስፈሪ ነው ብለዋል፡፡ ለደህንነቱ በመስጋት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ነዋሪ እንዳለው ከሆነ "ከዚህ ቀደምም ብዙ አስተያየት ሰጥተናል፤ ሰሚ ግን የለም። ህዝቡ ጦርነት ሰልችቶናል ፤ እስካሁን ያደረጋችሁት የእርስ በርስ ግጭት ይበቃችኋል ብሏል። ገላጋይ ነው ያጣነው " ብለዋል። ከትናንት በስቲያ ጀምሮ የደመወዝ ይከፈለን የሚሉ ጥያቄዎችን ይዘው ወደ ከተማዋ ገብተዋል የተባሉት ታጣቂዎች ላለፉት ሁለት ቀናት የፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤትን እንደከበቡ ናቸውም ተብሏል፡፡ ታጣቂዎቹ ከከልሉ ፕሬዝዳንት ጸህፈት ቤት በተጨማሪም የክልሉ መንግስት…
Read More
ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው በህወሀት ምክንያት መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ተናገሩ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በሰሜን እዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ለማሰብ በሚል በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ህወሀትን ተችተዋል። ፊልድ ማርሻል በዚህ ጊዜ እንዳሉት መከላከያ ሠራዊት ሕይወቱን ከሰጠለት ሕዝብ ውስጥ የወጡ ጥቂት ካሃዲዎች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ከኋላው መውጋታቸው ሕመሙ ጥልቅ ነው ብለዋል። በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈፀመው ክህደት ወንድም ወንዱሙ ላይ የፈፀመው ክህደት በመሆኑ በታሪክ ልዩ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። የትግራይ ሕዝብ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ክህደት አይቀበለውም ያሉት አዛዡ  የትግራይ ሕዝብ በልጆቹ ክህደት አፍሮ፣ ተመልሰን መቐለ ስንገባ አጨብጭቦ ተቀብሎን ነበር ሲሉም አክለዋል። ስለዚህ ክህደት እና አስነዋሪ ታሪክ ስናውራ ስለ ጥቂት የሕወሓት አመራሮች እንጂ ስለ ትግራይ ሕዝብ እንዳልሆነም ገልጸዋል። የህወሀት…
Read More
አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

በትግራይ ክልል በጊዜያዊ አስተዳድሩ እና በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ቡድን መካከል ግጭት መከሰቱን ተከትሎ የመፈንቅለ መንግስት እየተፈጸመ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ በመቀሌ እና አዲ አበባ በሰጧቸው መግለጫዎች ላይ እንዳሉት የህወሃት አንዱ ክንፍ በጊዜያዊ አስተዳድሩ ላይ አመራሮችን መሾም፣ ማህተም መቀማት፣ ቢሮዎችን መቆጣጠር እና ሌሎች ህጋዊ ያልሆኑ ስራዎችን እያካሄደ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ በትግራይ ክልል አለመረጋጋት የተፈጠረ ሲሆን በክልሉ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አይለዋል፡፡ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ከ20 በላይ ሀገራትም በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው ባወጡት የጋራ መግለጫ ላይ ገልጸዋል፡፡ የጋራ መግለጫውን ካወጡ ሀገራት መካከል አሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ጀርመን፣ፈረንሳይ፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም እና…
Read More
በትግራይ ዳግም ጦርነት ይቀሰቀሳል በሚል ነዋሪዎች ገንዘብ እና ምግብ ማከማቸት ጀምረዋል ተባለ

በትግራይ ዳግም ጦርነት ይቀሰቀሳል በሚል ነዋሪዎች ገንዘብ እና ምግብ ማከማቸት ጀምረዋል ተባለ

በትግራይ ዜጎች ዳግመኛ ግጭት ይቀሰቀሳል በሚል ስጋት ባለፉት ሶስት ቀናት ዉስጥ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ሸመታ ላይ ናቸዉ ተብሏል፡፡ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ክንፍ የተሾሙ የተባሉ ግለሰብ በሚሊሻዎች ታጅበው ትናንት የመቐለ 104 ነጥብ 4 ኤፍኤም ሬድዮ ጣብያ ለመቆጣጠር መሞከራቸው ተከትሎ በሬድዮ ጣብያው ውዝግብ ተፈጥሮ ነበር። ታጣቂዎቹ ከዚህ ቀደም በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተሾሙትን የጣቢያው ሃላፊ አውርደው በሌላ ሰው የመተካት እንቅስቃሴ ማድረጋቸውንና የከተማዋ ፖሊስ ደርሶ ድርጊቱን ማስቆሙ ታውቋል። የወታደራዊ አመራሮቹ ውሳኔ ተከትሎ ደግሞ ግጭት እንዳይነሳ የሰጉ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች ገንዘባቸው ከባንክ ማውጣት እና ሸቀጦች መግዛት ላይ ተጠምደዋል መባሉን ዶቼ ቬለ ዘግቧል። ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቐለ…
Read More
75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

75 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው ሊመለሱ ነው ተባለ

የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን እንዳስታወቀው በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ተሳትፎ ከነበራቸው 274 ሺህ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ቀድሞ ህይወታቸው እንደሚመልስ አስታውቋል፡፡ ከዚህ ውስጥም በመጀመሪያው ምዕራፍ 75ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝ የማድረግ ስራውን በነገው እለት በይፋ እንደሚጀመር ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ ፕሮግራምና ፕሮጀክቶች በመቅረጽ ከሰባት ክልሎች ከ371 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ከ760 ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በሁለት ዓመታት ውስጥ የዲሞቢላይዜሽንና መልሶ ማቋቋም ስራውን ለመጨረስ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮም ለመጀመሪያው ዙር ተዋጊዎች ብተና ማስፈጸሚያ ሀብት መንግስትና ከለጋሾች ማግኘት ተችሏል ተብሏል፡፡ መንግስት ኮሚሽኑ ስራ ሲጀምር 1 ቢሊዮን ብር የተለገሰ ሲሆን በተጨማሪም ከ7 ሀገራት 60 ሚሊየን ዶላር መገኘቱ ተገልጿል። በድጋፍ የአውሮፓ…
Read More
በሀገር ክህደት ወንጀል የሞት ፍርድ ተወስኖባቸው የነበሩ 178 ወታደሮች በይቅርታ ተለቀቁ

በሀገር ክህደት ወንጀል የሞት ፍርድ ተወስኖባቸው የነበሩ 178 ወታደሮች በይቅርታ ተለቀቁ

ወታደሮቹ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች የነበሩ ሲሆን አዲስ አመትን አስመልክቶ ይቅርታ ተደርጎላቸዋል ከሶስት ዓመት በፊት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ የሰሜን እዝ በህወሃት ታጣቂዎች መጠቃቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተቀሰቀሰው፡፡ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ይህ ያልታሰበ ጥቃት እንዲደርስባቸው አቀነባብረዋል የተባሉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት እና አመራሮች በሀገር ክህደት ወንጀል ተጠርጥረው ታስረው ነበር፡፡ እነዚህ 178 ወታደሮች በተመሰረተባቸው ክስ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የእድሜ ልክ እና ሞት ፍርድ ውሳኔ ተላልፎባቸው በእስር ላይ ነበሩ፡፡ በእስር ላይ የነበሩት የሠራዊት አባላቱ በፈፀሙት ወንጀል ተፀፅተው የይቅርታ ጥያቄአቸውን ለመንግስት እና ለመከላከያ ሚኒስቴር አሥገብተዋል ተብሏል። ወታደሮቹ የይቅርታ ጥያቄ ማስገባታቸውን ተከትሎ በአንድ በኩል ጉዳያቸው ለይቅርታ ቦርድ…
Read More
በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ተጠየቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ተጠየቀ

በሁለት አመቱ የትግራይ ጦርነት የተፈፀሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ጥሪ አቀረበ። የያለፈው ጦርነት እና ጥፋት ተጠያቂነት ባለመረጋገጡ በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ሐይሎች ለሌላ ጥፋት እየተዘጋጁ ነው በማለት አረና ከሷል። በወቅታዊ የትግራይ ፖለቲካዊ ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙርያ መግለጫ የሰጠው በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ህወሓት ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል ለትግራይ አደጋ ይዞ የሚመጣ እና ሐላፊነት የጎደለው አካሄድ እየተከተለ ያለ ሲል ገልፆታል። የዓረና ትግራይ ሊቀመንበር አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ "አሁንም ወደ ጦርነት የሚወስዱ መንገዶች እየታዩ ያሉት እና የጦርነት ነጋሪት የሚጎሰመው ባለፈው 2 ዓመት ለነበረው ጦርነት ከሁሉም ወገን ተጠያቂነት ባለመረጋገጡ ነው፤ ከህወሓት ይሁን ከሻዕብያ እንዲሁም ብልፅግና ወገን የጦርነቱ…
Read More
ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ "የህወሓት ኃይሎች" ከሱዳን ጦር ጎን በቅጥረኝነት ተሰልፈው ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጋር እየተዋጉ ነው መባሉን አስተባብሏል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በትናትናው እለት ባወጣው መግለጫ የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር እና ተባባሪ ሚሊሻዎች ጋር ሆነው እየተዋጉት እንደሆነ ማረጋገጡን መግለጹን ተከትሎ ነው። የሱዳን ጦርነት ከተጀመረበት ከሚያዝያ 2023 ወዲህ የሱዳን ጦር የውጭ ቅጥረኞችን እርዳታ እየፈለገ ነው የሚል ክስ ያቀረበው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጦር፣ በጦርነት ወቅት ተገድለው የተገኙ ቅጥረኞችን መመዝገቡን ጠቅሷል። የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ጎን ተሰልፈው  እየተዋጉ ነው የሚለውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች "መሰረተ ቢስ ክስ" በጽኑ እንደሚያወግዝ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደገለጸው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች…
Read More