04
Oct
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያ ሆን ብላ ጎርፍ እንዲፈጠር ውሃ እየለቀቀች ነው ሲሉ ከሰዋል፡፡ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ ኢትዮጵያ “በሶማሊያ ጎርፍ እንዲከሰት ሆን ብላ ከግድቦቿ ውሃ እየለቀቀች ነው” ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ከዘኢኮኖሚስት ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፤ በሶማሊያ በጎርፍ የተጥለቀለቁ አካባቢዎችን ፎቶግራፎች አቅርበው፤ አደጋው ኢትዮጵያ ሆን ብላ ያደረገችው ነው ሲሉ ከሰዋል። ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ ኢትዮጵያ በድንበር አቅራቢያ “በጎሳ ለተመሰረቱ ለሶማሊያ ሚሊሻዎች ትጥቅ እያስተላለፈች ነው” ሲሉም ተጨማሪ ክስ አቅርበዋል። እነዚህ መሳሪያዎች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሰው “በአልሸባብ እጅ ሊወድቁ ይችላሉ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። አክለውም ኢትዮጵያ “የግብፅ ወታደሮች ስምሪትን እንዲቃወሙ በሶማሊያ ውስጥ ያሉ የጎሳ መሪዎችን እና የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን እያበረታታች ነው” ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ባሳለፍነው ጥር ወር…