Ethiopia

የቻይናው ጓንዡ አውቶሞቢል ግሩፕ በኢትዮጵያ መኪና ማምረት እንዲጀምር ተጠየቀ

የቻይናው ጓንዡ አውቶሞቢል ግሩፕ በኢትዮጵያ መኪና ማምረት እንዲጀምር ተጠየቀ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ኩባንያው ከሽያጭ ማዕከል መክፈት በተጨማሪ የማምረቻ እና መገጣጠሚያ ማዕከልም እንዲከፍት ጠይቀዋል። GAC JUNTU አዲስ ዘመናዊና ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሠራ የትራንስፖርት ሥርዓት በማስተዋወቅ፣ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ቀዳሚ የኤግዚቢሽን ማዕከሉን በአዲስ አበባ በይፋ መርቋል። የኩባንያው  የምርት ማሳየ 2,300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው  ሲሆን ከማሳያነት ባለፈ  ከሽያጭ በኋላ  አገልግሎት፣  መለዋወጫ እና በአምራች የተደገፈ ዋስትና የሚሰጥበት አካቷል ተብሏል። ተቋሙ የተሽከርካሪ ሽያጭን፣ የተረጋገጠ የድኅረ-ሽያጭ አገልግሎትን፣ ኦሪጅናል የመለዋወጫ ዕቃዎችን እና ከአምራቹ የሚሰጥ ዋስትናን ያካተተ የተሟላ የ4S-ደረጃ ሥርዓት (4S-standard ecosystem) በማቅረብ በኢትዮጵያ ለታማኝነትና ለደንበኞች አገልግሎት አዲስ መለኪያ ያስቀምጣል። GAC JUNTU የኢትዮጵያን ገበያ  አራት ዘመናዊ  የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ይዞ መቅረቡን…
Read More
ጊፍት ሪልስቴት ከ1200 በላይ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ

ጊፍት ሪልስቴት ከ1200 በላይ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ

በኢትዮጵያ የቤት ልማት ፕሮግራም ወይም ሪልኢስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ አንዱ የሆነው ጊፍት ሪል ስቴት በ15 በመቶ ቅናሽ ለፋሲካ በዓል የአፓርትመንትና የንግድ ሱቆችን ለሽያጭ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡ የድርጅቱ ሽያጭ እና ማርኬቲንግ ዳይሬክተር አቶ ብርቁ ይርጋ በአዲስ አበባ ለገሀር ሳይት በተዘጋጀ ፕሮግራም ላይ እንዳሉት ጊፍት ሪል ኢስቴት ደንበኞች የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በ2 በመቶ ቅድመ ክፍያ ብቻ ቤት መግዛት እንዲችሉ የሚያስችል ኤክስፖ ማዘጋጀቱን ገልፀዋል። የሽያጭ ኤክስፖው ከመጋቢት 19 እስከ ሚያዚያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን 1 ሺህ 200 ቤቶች ለሽያጭ መቅረባቸውን ዳይሬክተሩ ተገልጿል። በ2005. የተመሰረተው ጊፍት ሪል ስቴት ሦስት መንደሮችን ጨርሶ ለገዢዎች አስረክቧል የተባለ ሲሆን አራተኛውን የጊፍት ሜትሮፖሊታን መንደር በለገሃር ላይ 4 ሺህ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ የኢንሹራንስ ባለአክሲዮኖችን ለመመዘን አዲስ መመሪያ አወጣ

ብሔራዊ ባንክ የኢንሹራንስ ባለአክሲዮኖችን ለመመዘን አዲስ መመሪያ አወጣ

ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ በኢንሹራንስ ዘርፉ ላይ ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን እና የተጠናከረ የኮርፖሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያለመ ነው ብሏል። በዚህ መመሪያ መሠረትም ማንኛውም የኢንሹራንስ ኩባንያ የቦርድ አባላት ስብጥር አንድን ጾታ ብቻ የያዘ መሆን የለበትም። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ቢያንስ ሁለት ሴት የቦርድ አባላት ሊኖሩት እንደሚገባ መመሪያው የግዴታ መስፈርትን አስቀምጧል። በተጨማሪም አንድ የቦርድ አባል ለመሆን ዝቅተኛው የዕድሜ ገደብ 30 ዓመት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ሦስት ገለልተኛ የቦርድ አባላት ሊኖሩት ይገባል የተባለ ሲሆን እነዚህ ግለሰቦች የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው እና በፋይናንስ ዘርፍ ወይም ተያያዥ መስኮች የ10 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል ተብሏል። እንደ መመሪያው ከሆነ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች በገለልተኛ የቦርድ…
Read More
በተፈጥሮ ጋዝ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች አዲስ አስገዳጅ ደረጃዎች መውጣቱ ተገለጸ

በተፈጥሮ ጋዝ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች አዲስ አስገዳጅ ደረጃዎች መውጣቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ መጠቀም መጀመሯን ተከትሎ አስገዳጅ ደረጃዎች ማዘጋጀቱን ገልጿል። የኢንስቲትዩቱ ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ በሰጡት መግለጫ 79 አጠቃላይ ደረጃዎችን መዘጋጀታቸውን ገልጸው ከዚህ ውስጥ ሰባቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ደረጃዎች እንደሆኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት በሀገር ውስጥ ለሚገጣጠሙ እና ከውጭ ለሚገቡ በነዳጅ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ደረጃዎች እንዳሏት የተናገሩት ዶክተር መሰረት በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ግን የሚመዘኑበት የጥራት ማስጠበቂያ ደረጃ እንዳልነበራት አክለዋል፡፡ አዲሱ ደረጃ የተፈጥሮ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ሲገጣጠሙ ሊሟሉ የሚገቡ መስፈርቶችን የያዘ እንደሆነም ተገልጿል። በኢንስቲትዩቱ የደረጃዎች ዝግጅት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ይልማ መንግስቱ በሰጡት ተጨማሪ ማብራሪያ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ጥራት ለማስጠበቅ የወጣው ደረጃ በሶማሊ ክልል የተገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ መጠቀም በመጀመሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ አዲሱ ደረጃ የተፈጥሮ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚገባቸው…
Read More
ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ግብር የድጅታል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ተስማማ

ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ግብር የድጅታል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ተስማማ

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የታክስ ክፍያዎችን በኤም-ፔሳ የዲጂታል ስርዓት ለመሰብሰብ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ በሆነው ኤምፔሳ_ኢትዮጵያ እና የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ መካከል በባህር ዳር ከተማ ተፈርሟል። ግብር ከፋዮች ከዚህ በኋላ ኤም-ፔሳን በመጠቀም ግብራቸውን ካሉበት ሆነው በዲጂታል አማራጭ በቀላሉ መክፈል ይችላሉ ተብሏል። ከ477 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ያሉት የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2017 የግብር ዘመን 67 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) ተናግረዋል። በ2018 በጀት ዓመትም ክልሉ 100.37 ቢሊየን ብር የመሰብሰብ እቅድ ያለው ሲሆን ከዚህ ውስጥ እስካሁን 60 በመቶ የሚሆነውን ሰብስቧል ብለዋል። የታቀደውን ገቢ መሰብሰብ የሚቻለው በዲጂታል አማራጭ በመታገዝ ግብርን በቀላሉና…
Read More
በአዲሱ የነዳጅ አቅርቦት መመሪያ መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸው እነማን ናቸው?

በአዲሱ የነዳጅ አቅርቦት መመሪያ መሰረት ቅድሚያ የሚሰጣቸው እነማን ናቸው?

የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን በመካከለኛው ምስራቅ ያጋጠመውን ጦርነት ተከትሎ ዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን የነዳጅ አቅርቦት መስተጓጎል ለመቋቋም በአገር ውስጥ የነዳጅ ስርጭት እና ግብይት ላይ ጥብቅ የቁጠባ እርምጃዎች እንዲወሰዱ የሚያዝ አዲስ መመሪያ አውጥቷል። በመመሪያው መሠረት የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ለማንኛውም የነዳጅ ዓይነት አቅርቦት ቅድሚያ እንዲሰጡ ያላቸውን አካላት ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ለፀጥታ ተቋማት፣ ቁልፍ ለሆኑ የመንግስት ፕሮጀክቶች እና በተለይም በመጠናቀቅ ላይ ላሉ የልማት ስራዎች ቅድሚያ እንዲሰጣቸው አዟል። ለኢንዱስትሪዎች፣ መሠረታዊ ሸቀጦችን ለሚያመርቱ አምራች ድርጅቶች እና ምርታቸውን ወደ ውጭ ለሚልኩ ተቋማትም ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ከተባሉ አካላት መካከል ናቸው። እንዲሁም ከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለሚታይባቸው እና የሀገር አቋራጭ የትራንስፖርት ፍሰት ላለባቸው የኮሪደር አካባቢዎች እና ለሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች…
Read More
ኢትዮጵያ የ4 ቢሊዮን ዶላር ማዕድን ኢንቨስትመንት ተፈራረመች

ኢትዮጵያ የ4 ቢሊዮን ዶላር ማዕድን ኢንቨስትመንት ተፈራረመች

በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ የተገለጸ የብረን ማዕድን በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ጊምቢ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለማውጣት ስምምነት ተፈርሟል፡፡ የማዕድን ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና ቻይናዊያን በተቋቋሙ ኩባንያዎች መካከል የብረት ማዕድን ልማት ፕሮጀክት ዛሬ ተፈራርሟል፡፡ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ አለው የተባለው ይህ የ10 ዓመት የብረት ማዕድን ማውጣት ስምምነት የማዕድን ሚኒስቴር እና ዜድ ዋይ ቲቢ-ዲኤይኤም ስቲል ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ የግል ኩባንያ ጋር ስምምነት ፈጽሟል፡፡ የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ከስምምነቱ በኋላ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የብረት ማዕድናት እንዳሏት ካወቀች ከ70 ዓመት በላይ ቢሆናትም “እስካሁን አንድም የብረት ማዕድን አለማውጣቷን” ተናግረዋል፡፡ “በወለጋ ጊምቢ ቢቂላል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ብረት እንዳለን የታወቀው በ1956 ነበር፣ ግን እንደምታውቁት እስካሁን አንድም ብረት ማዕድን…
Read More
በጋሞ ዞን ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱ ተገለጸ

በጋሞ ዞን ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱ ተገለጸ

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ፣ካምባ እና ቦንኬ በተባሉ ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱን የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ተናግረዋል። ‎ከሟቾቹ መካከል ከጋጮ ባባ ወረዳ ብቻ 102፣ ከካምባ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቦንኬ ወረዳ 3 በድምሩ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስተዳዳሪው ገልጸዋል። አስተዳዳሪው አክለውም እስካሁን በተከናወነው አስቸጋሪ ፍለጋ የ57 ሰዎች አስክሬን መገኘቱንና በጋጮ ባባ ወረዳ የቀሪ 50 ሰዎች አስክሬን እየተፈለገ መሆኑን ተናግረዋል። ‎የአከባቢው መልካምድር አስቸጋሪ መሆን አስክሬን ፍለጋውን ከባድ ማድረጉን የገለፁት የዞኑ አስተዳዳሪው ጉዳት ለደረሰባቸውና ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። ‎የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት በበኩሉ የአደጋ መከታተያ…
Read More
የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣውን ገንዘብ ጨምሮታል ተባለ

የእስራኤል- ኢራን ጦርነት ለነዳጅ ድጎማ የሚወጣውን ገንዘብ ጨምሮታል ተባለ

ኢትዮጵያ ለነዳጅ ግዢ በየዓመቱ ከ4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወጪ እንደምታደርግ ተገልጿል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ዛሬ መጋቢት 2፣ 2018 በሰጡት መግለጫ በእስራኤል-አሜሪካ እና ኢራን መካከል በተጀመረው ጦርነት ምክንያት ለነዳጅ ድጎማ የሚያወጣው ወጪ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አህመድ ገለጻ ይህ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ አንድ ሊትር ቤንዚን በ129 ብር ለተጠቃሚዎች ስታቀርብ የነበረ ሲሆን ድጎማው ቢቀር ግን የአንድ ሊትር ቤንዚን መሸጫ ዋጋ 157 ብር ይሆን ነበር፡፡ እንዲሁም ነጭ ናፍጣ 129 ነበር በሊትር ሲሸጥ ነበር የተባለ ሲሆን ድጎማው ቢነሳ 182 ነጥብ 8 ብር መሸጥ ነበረበት ተብሏል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ኢትዮጵያ ቤንዚን የ28 ነጥብ…
Read More
የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60 ሰራተኞቹ እንደተገደሉበት አስታወቀ

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን 60 ሰራተኞቹ እንደተገደሉበት አስታወቀ

የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ባለፉት 60 ዓመታት ቢያንስ 60 ሠራተኞቹን በሥራ ላይ እያሉ ህይወታቸውን እንዳጡ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ባለፉት 6 አሥርት ዓመታት የዱር እንስሳትን እና የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅ ሂደት ውስጥ ቢያንስ 60 ሠራተኞቹ በሥራ ላይ እያሉ ሕይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቋል። ባለሥልጣኑ ዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የ60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን የፊታችን መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚያከብር አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩመራ ዋቅጅራ፣ ሠራተኞቹ ሕይወታቸውን ያጡት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጋር በተያያዙ የተለያዩ የሥራ ላይ ፈተናዎች መሆኑን ገልጸዋል። ባለሥልጣኑ ባለፉት 60 ዓመታት ውስጥ ከ1 ሺህ 700 በላይ ለሚሆኑ ልዩ ልዩ የዱር እንስሳት ዝርያዎች ጥበቃ…
Read More