Business

ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው ልማት ባንክ እና አማራ ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሀንስ አያሌው በኪሳራ ላይ ላለው ጸደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ተደርገው ተሾመዋል። የአማራ ብድርና ቁጠባ ድርጅት በሚል ሲጠራ የነበረው በኋላም ጸደይ ባንክ በሚል ስያሜ የኢትዮጵያን የባንክ ቢዝነስ የተቀላቀለው ጸደይ ባንክ በኪሳራ ላይ ይገኛል። ባንኩ በ2024/25 በጀት ዓመት ብቻ የሁለት ቢሊዮን ብር ኪሳራ እንደደረሰበት ከአንድ ወር በፊት ዓመታዊ ጉባኤውን ሲያካሂድ ገልጿል። ይህን ተከትሎም ዶክተር ዮሀንስ አያሌው የባንኩ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆነው እንደተሾሙለት ባንኩ ከደቂቃዎች በፊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስታውቋል። በኪሳራ ላይ ያሉ የገንዘብ ድርጅቶችን በመታደግ የሚታወቁት ዶክተር ዮሀንስ ከዚህ በፊት ልማት ባንክን እንዲሁም የአማራ ባንክን ከኪሳራ ወደ ትርፍ መመለሳቸው ይገለጿል። ላለፉት ዓመታት ጸደይ ባንክን በፕሬዝዳንትነት…
Read More
ፓርላማው የሞርጌጅ ባንክ ዳግም እንዲቋቋም ጠየቀ

ፓርላማው የሞርጌጅ ባንክ ዳግም እንዲቋቋም ጠየቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሞርጌጅ ባንክ ወይም የቤት ብድር ባንክን ሀላፊነት ወስዶ መልሶ እንዲያደራጅ ጠይቋል፡፡ በሀገሪቱ ቀድሞ የነበረዉ የሞርጌጅ ባንክ ባልታወቀ ምክንያት ወደ ንግድ ባንክ መቀላቀሉ ስህተት መሆኑ ተገልጿል። ፓርላመው ይህን የተጠየቀዉ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በገመገመበት ወቅት ነው። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ፣ መሠረተ-ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ መሃመድ አብዶ በግምገማዉ ወቅት መንግስት በቤቶች ልማት ላይ ያለውን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት የሞርጌጅ ባንክ መልሶ ማደራጀት አለበት ሲሉ ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ቀደም ባሉት ዘመናት የቤት ብድር ባንክ ሞርጌጅ እንደነበረና ባልታወቀ ምክንያት ፈርሶ ወደ ንግድ ባንክ የተቀላቀለ መሆኑን የቋሚ…
Read More
ኢትዮጵያ ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርትን ለዓለም ገበያ አስተዋወቀች

ኢትዮጵያ ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርትን ለዓለም ገበያ አስተዋወቀች

ኦሪጅናል ቴፍ-ሊ የተባለው ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርት ዛሬ በለንደን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና በአምራቾቹ ትብብር በተዘጋጀ የማስተዋወቂያ መድረክ ላይ ይፋ ተደርጓል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ከንግድ ማህበረሰቡ፣ ከሚዲያ፣ ከእንስሳት ተዋጽኦዎች ነፃ በሆኑ ምግቦች ምርት እና ግብይት ውስጥ የሚሳተፉ ኢንዱስትሪዎች አባላት እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከእፅዋት የተዘጋጁ የምግብ አማራጮች ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ዝግጅቱ ጤፍን ለአለም አቀፍ ታዳሚዎች የበለጠ ለማስተዋወቅ እድል ፈጥሯል። በብሪታንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በመክፈቻ ንግግራቸው ጤፍ በኢትዮጵያዊያን የአመጋገብ ዘይቤ ውስጥ ያለውን ሰፊ ቦታ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚችሉ የምግብ ስርዓቶች ጥናቶች ላይ ሊያበረክት ስለሚችለው አዎንታዊ አስተዋጽኦ አብራርተዋል፡፡ የኦሪጅናል ቴፍ-ሊ (The Original Teff-ly) መስራቾች…
Read More
ባለፉት 6 ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ

ባለፉት 6 ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ

ኢትዮጵያዊ ባለፉት ስድስት ወራት እንደ ሀገር ከ704 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ እንደተቻለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።  አፈጻጸሙ በገቢዎች ሚኒስቴር በግማሽ ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው 640 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ውስጥ 704 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 110 በመቶ ተሳክቷል ተብሏል። ይህ ገቢ ባለፉት ጊዜያት ለዓመታት ሲሰበሰብ ከነበረው ገቢ ጋር የሚመሳሰል እንደሆነ ተገልጿል። የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ዓመት ስድስት ወራት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ63 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን ስኬቱ ኢትዮጵያ የውስጥ አቅሟን በማጎልበት እያንሰራራች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ ተድርጎ የሚወሰድ ነው ሲል መንግሥት አስታውቋል። በግማሽ ዓመቱ ከሀገር ውስጥ ታክስ 362 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን ከውጪ ንግድ…
Read More
የቡና ግብይት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ውጭ በስፋት እንደሚካሄድ ተገለጸ

የቡና ግብይት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ውጭ በስፋት እንደሚካሄድ ተገለጸ

ለውጭ ገበያ የማይውሉ ና የተመለሱ ምርቶች ግብይት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ብቻ በኩል እንዲሸጡ አስገዳጅ አሰራር ቢዘረጋም ምርቶቹ መዳረሻቸዉ እየታወቀ አይደለም ተብሏል። ከዉጪ ገበያ የሚመለሱት ምርቶች ግብይት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ አማካኝነት መሆን እንዳለበት ቢቀመጥም ይህ ተግባራዊ እየተደረገ እንዳልሆነ ተገልጿል። የፌደራል ዋና ኦዲተር እንዳስታወቀው ቡናን ጨምሮ ሁሉም ምርቶች መዳረሻቸዉ እየታወቀ አለመሆኑን ተናግሯል። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምርት ቅበላ፣ ክምችት እና የግብይት ሥርዓት አፈፃፀምን በተመለከተ የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት ላይ ማብራሪያ ጠይቋል። ከዉጪ ገበያዉ የሚመለሰዉን እና የማይወለዉን ምርት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ሻጭ እና ገዥን የማገናኘት ሀላፊነት በግብይቱ ላይ እየታየ አይደለም ሲሉ የፌደራል ዋና ኦዲተር…
Read More
ኢትዮጵያ ሁሉንም የስፖርት ውርርድ ቤቶች ፈቃድ ሰረዘች

ኢትዮጵያ ሁሉንም የስፖርት ውርርድ ቤቶች ፈቃድ ሰረዘች

በኢትዮጵያ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ሲሰሩ የቆዩ የሁሉም የስፖርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃድ መሰረዙ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ሁሉንም የስፖርት ውድድር ውርርድ ድርጅቶች የሥራ ፈቃዶች ከታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መሰረዛቸውን ገልጿል። የፈቃድ ስረዛው በውርርድ እና በፋይናንስ ዘርፉ ላይ በተካሄደ አገር አቀፍ ጥልቅ ግምገማ ላይ ተመስርቶ የሕዝብን ጥቅም ለማስከበር የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል። ውሳኔው በስራ ላይ ባሉትና ቀደም ሲል በይፋ በታገዱት በሁሉም የውርርድ ድርጅቶች በእኩልነት ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሂደት ላይ ያለው ምርመራ በዘርፉ ውስጥ የተንሰራፋ ሀገ-ወጥ አሰራር፣ የፈቃድ ውል ጥሰት እና ለብሔራዊ ደህንነት ስጋት የሚሆኑ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውሮች እንዳሉ በግልጽ አመላክቷል። ለስፖርት ውርርድ ድርጅቶች እና ሲስተም…
Read More
በኢትዮጵያ ዓመታዊ የድጅታል ገንዘብ ልውውጥ ከ18 ትሪሊዮን ብር በላይ ደረሰ

በኢትዮጵያ ዓመታዊ የድጅታል ገንዘብ ልውውጥ ከ18 ትሪሊዮን ብር በላይ ደረሰ

ብሔራዊ ባንክ እንዳስታወቀው በአንድ አመት ውስጥ በጂታል ክፍያ ስርአት 18 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ዝውውር ተፈጽሟል። በኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ኮንፈረንስ 2.0. ላይ ለአምስት አመት የሚቆይ (2026-30) የብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ በብሔራዊ ባንክ ይፋ ሆኗል። የመጀመሪያው የ2021-24 ብሄራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ ላይ ህግ ማውጣት፣ተቋማት አገልግሎቱን እንዲሰጡ ማስቻልና ቁጥጥርና ክትትል ማድረግ እንዲሁም መሠረተ ልማት ዝርጋታ መከናወናቸው ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የክፍያ ስርአት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ዳምጠው ለቅዳሜ ገበያ እንደገለጹት በኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ትልቁ ሚና የገንዘብ ዝውውር ፈጣን ቀልጣፋ ወጪ ቆጣቢ መሆን አለበት። ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ የዲጂታል የክፍያ ስርአትን ማዘመን እና ለዚያ የሚያበቃ የድጅታል መሰረተ ልማት ግንባታ ጉልህ ሚና ይጫወታል። ባለፈው አንድ አመት…
Read More
ያንጎ  በኢትዮጵያ መተገበሪያው ላይ አዲስ የደንበኛ ደህንነት መጠበቂያ ማከሉን ገለጸ

ያንጎ  በኢትዮጵያ መተገበሪያው ላይ አዲስ የደንበኛ ደህንነት መጠበቂያ ማከሉን ገለጸ

የአለምዓቀፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የያንጎ ግሩፕ አካል የሆነው ያንጎ ራይድ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚያገለግለው መተግበሪያው ውስጥ የሚገኘውን የደንበኛ ደህንነት መጠበቂያ አሻሽያለሁ ብሏል። ተሻሻለው መተግበርያ እያንዳንዱ ተጓዥ ዝርዝር የደህንነት መስፈርቶች መሟላታቸውን የሚያረጋግጥበት አገግሎግሎት፥ በወቅታዊ የጉዞ ሁኔታ መረጃ ላይ ተመስርቶ ምን አይነት የደህንነት እርምጃዎች መወሰድ እንደሚገቡ መረጃ የሚሰጥ እንዲሁም ስለ ጉዞ ደህንነት አጠቃላይ የደህንነት መረጃዎች የሚሰጥ የማዕከል አገልግሎት የተካተተበት ነው ተብሏል።አዲሱ የደህንነት ማዕከል የመተግበሪያውን አጠቃቀም ማንበብ፣ የግል መረጃን መሙላት ፣ የሚያምኗቸውን ሰዎች ስልክ ቁጥር መሙላት፣ የራስን ፎቶ ማንሳት እና ኢ-ሜል መቀየርን የመሳሰሉ ተሳፋሪዎች መሙላት ያለባቸውን ዝርዝሮችም ይይዛል።ከዝርዝሩ ውስጥ የጎደለ ነገር ካለ መተግበሪያው ያልተሞላው ላይ ምልክት በማድረግ ተሳፋሪው እንዲሞላው ይጠይቃል። ተሳፋሪዎች የአጋር አሽከርካሪዎችን ስታንዳርድ፣ አደጋ…
Read More
ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ገልጿል። መ/ቤቱ ፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን መቆየቱን አመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹ ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት ባለመስራት፣ በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው፣ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው ተገኝተዋል ተብሏል። ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል ሲል…
Read More
ኢትዮጵያ ከሁሉም ጎረቤት ሀገራት ጋር የባቡር ትራንስፖርት የመገንባት እቅድ እንዳላት ገለጸች

ኢትዮጵያ ከሁሉም ጎረቤት ሀገራት ጋር የባቡር ትራንስፖርት የመገንባት እቅድ እንዳላት ገለጸች

የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠናን ታሳቢ ያደረገ የባቡር መስመር ትስስር ወደ ሁሉም የጎረቤት ሀገራት እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል። የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ታሳቢ ያደረገ እና ኢትዮጵያን ከሁሉም የጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስር የባቡር መስመር እየተሰራ እንደሚገኝ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር አስታውቋል። የባቡር ትራንስፖርት ኢንቨስትመንት ከፍተኛ በመሆኑ ረዥም ርቀትን፣ መሰረተ ልማትን እንዲሁም ንግድና ቀጠናዊ ትስስርን ታሳቢ አድርጎ እንደሚሰራ የገለፁት የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ናቸው። በመሆኑም የባቡር መስመር ዝርጋታ በሀገር ውስጥ የሚቆም ሳይሆን፤ በሁሉም አቅጣጫ ከሚገኙ ጎረቤት ሀገራትና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ ለመነገድና ለመስራት የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል። ከጎረቤት ሀገራት ባሻገር ደግሞ የአፍሪካን አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ከማስፋፋት አንፃር ታሳቢ ያደረገ…
Read More