አካባቢ ጥበቃ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሚሰጠው የብድር ወለድ ላይ ማሻሻያ አደረገ

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሚሰጠው የብድር ወለድ ላይ ማሻሻያ አደረገ

ባንኩ በግብርና ስራዎች ለተሰማሩ ተበዳሪዎች የብድር ወለድ መጠኑን ከ11 በመቶ ወደ 7 በመቶ ዝቅ ማድረጉን አስታውቋል። ባንኩ በኢትዮጵያ የግብርና ስራዎችን ለማበረታታት በሚል ለተበዳሪዎች በሚሰጠው ብድር ላይ ያስከፍል በነበረው ወለድ ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ገልጿል። የብድር ወለድ ቅናሽ የተደረገው ያ ያልታረሰን የመሬት ሀብት ወደ ስራ ለማስገባት፤ ባለሀብቶች፣ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች የበለጠ እንዲበረታቱ ለማድረግ በማሰብ እንደሆነ አስታውቋል። በዚህም መሰረት በአነስተኛ፣ መካከለኛና የኮርፖሬት ፕሮጀክት ብድር ለሚጠይቁ ይጠበቅ የነበረው የ11.5 በመቶ የማበደሪያ የወለድ ተመን ወደ 7 በመቶ ዝቅ አድርጓል ብሏል። ልማት ባንክ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለማሳደግ እና ከውጭ ተመርተው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት በሚል የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት…
Read More
ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እንደገለጸው ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የመስኖ ግድቦች ውስጥም 13ቱን በተያዘው የ2016 ዓመት በከፊል ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ ዓመት እንዲጠናቀቁ በሚል እየተገነቡ ላሉ ግድቦችም 8 ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ 28 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 13 የመስኖ ፕሮጀክቶች በከፊል ሲጠናቀቁ 2 ሺህ 450 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ እንደሆኑም ሃለፊው ተናግረዋል፡፡ እየተገነቡ ካሉት ግድቦች በተጨማሪም 27 አዲስ የመስኖ ግድቦችን ለመገንባት የጥናትና ዲዛይን…
Read More
ኢትዮጵያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ልታግድ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ልታግድ መሆኗን ገለጸች

በአዲስ አበባ ከፍተኛ ጭስ የሚለቅ መኪና ያላቸው አሽከርካሪዎች አስቀድመው መፍትሄ እንዲያዘጋጁ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ ተሸከርካሪዎች የሚለቁትን ጭስ የሚለካ መሳሪያ እና ጥራት ማስጠበቂያ ወይም ስታንዳርድ በመዘጋጀት ላይ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ድዳ ድሪባ እንደተናገሩት የመኪና ጭስ ስታንዳርድ እየተዘጋጀ ነው የተባለ ሲሆን እያንዳንዱ መኪና የሚያስወጣው ጪስ ይለካል ተብሏል። መኪናው ከተቀመጠው መለኪያ በላይ ጪስ የሚያመነጭ ከሆነ አገልግሎት እንዳይሰጥ ይደረጋል ብለዋል። አብዛኛውን ጊዜ ከፍተኛ ጭስ የሚለቁ ተሽከርካሪዎች ከተመረቱ 23 ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገሉ ናቸው ያሉት ኃላፊው፤ ስለዚህ አሮጌ መኪና ያላቸው አሽከርካሪዎች ከአሁኑ መፍትሄ ሊያዘጋጁ ይገባል ብለዋል። በመዲናዋ አሮጌና ከፍተኛ ጭስ የሚለቁ በርካታ መኪኖች መኖራቸውን…
Read More
በኢትዮጵያ የአህያ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የአህያ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ

በአህያ ደህንነት ዙሪያ የሚሰራው ብሩክ ኢትዮጵያ የተሰኘው የእንስሳት መብት ተሟጋች ድርጅት የአህያ ቁጥር እየቀነሰ መሆኑን ገልጿል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ሀገራት መላክ የተጀመረ ሲሆን ዓላማውም የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት እንደሆነ ይገለጻል፡፡ በዚህ የአህያ እርድ3 እና ንግድ ምክንያት የአህያ ቁጥር እየቀነሰ መምጣቱን እና ይህም እንዳሳሰበው ብሩክ ኢትዮጵያ የተሰኘ የአህያ መብት ተሟጋች ድርጅት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ አህያ እንዲታረድ እና ስጋና ቆዳው ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መደረጉ እንደ አገር የአህያ ቁጥር እየተመናመነ እንዲመጣ ማድረጉን የብሩክ ኢትዮጵያ ድርጅት አማካሪ ይልማ አበበ ለመናኃሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በኢትጵያ የአህያ እርድ በቻይና ባለሃብቶች በመስፋፋቱ ለአገር የውጭ ምንዛሪን ቢያስገኝም፤ እንደ አገር የአህያ መኖር ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ ደረጃ ላይ…
Read More
አየርላንድ ለኢትዮጵያ የምግብ ደህንነት 8.4 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማማች

አየርላንድ ለኢትዮጵያ የምግብ ደህንነት 8.4 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማማች

የገንዘብ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር እና የአየርላንድ መንግሥት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የ8 ሚሊየን 400 ሺሕ ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የፈረሙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ እና የአየርላንድ የዓለም አቀፍ ልማትና ዳያስፖራ ሚኒስትር ዴዔታ ሾን ፍሌሚንግ ናቸው፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱ ሦስት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው 5 ሚሊየን ዩሮ ለሴፍቲ ኔት ፕሮግራም እንዲሁም 3 ሚሊየን ዩሮ በጤና ላይ ያተኮሩ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጽልል። እንዲሁም 400 ሺሕ ዩሮ ደግሞ ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር ድጋፍ እንደሚውል በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ከፊርማ ሥነ- ሥርዓቱ በኋላ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ አየር ላንድ ለኢትዮጵያን የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እያደረገችው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡ ሦስቱም ስምምነቶች በመንግሥት…
Read More
ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ሀይል እንደምትሽጥ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ሀይል እንደምትሽጥ ገለጸች

የኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 30 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሁለት ሺህ ከ993 በላይ ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ይደረጋል፡፡ ለሦስት ጎረቤት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ለሱዳን፤ ኬንያ እና ጅቡቲ 2 ሺህ 993 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት በማድረግ 182 ሚሊዮን ዶላር ወይም 10 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል፡፡ ለሀገር ውስጥ ደንበኞች በሚሸጥ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 20 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት መታቀዱንም አቶ ሞገስ ተናግረዋል፡፡ ባሳለፍነው የ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት…
Read More
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራ በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራ በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች እና ፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ከሁለት ወራት የእረፍት ጊዜ በኋላ ተከፍቷል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በምክር ቤቶቹ የመክፈቻ ንግግራቸው ላይ የመንግስትን የአንድ ዓመት የትኩረት መስኮች ይፋ አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ በንግግራቸው ላይ ያለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ግድብ 4ኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠረናቀቁ ትልቁ ስኬት ነበር ብለዋል፡፡ 90 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀው የህዳሴው ግድብ የሲቪል ምህንድስና ስራ ሙሉ ለሙሉ በዚህ ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል፡፡ ይህ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ የሚያመነጭ ግድብ ሳይሆን የቱሪዝምና የውሃ ሀብት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሞራል ልዕልና ነው ብለዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ አክለውም መንግስት በተያዘው ዓመት የሕግ የበላይነትን ማስከበር፣ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የስራ እድል ፈጠራ ፣ የምግብ ዋስትና እና መልካም አስተዳድር ልዩ ትኩረት…
Read More
ሶስተኛው የህዳሴው ግድብ ድርድር በካይሮ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ሶስተኛው የህዳሴው ግድብ ድርድር በካይሮ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ባሳለፍነው ሐምሌ ወር ላይ በሱዳን ለተከሰተው ጦርነት እልባት ለመፈለግ በሚል በካይሮ በተካሄደው የጎረቤት ሀገራት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ጋር የህዳሴው ግድብ የሶስትዮሽ ድርድርን ለማስቀጠል መስማማታቸው ተገልጾ ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት ከሶስት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪ የቴክኒክ ባለሙያዎች በግብጽ ካይሮ ተገናኝተው ተወያይተዋል። እንዲሁም ሁለተኛው ዙር የቴክኒክ ባለሙያዎች ውይይት ደግሞ ባሳለፍነው ቅዳሜ እና እሁድ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ዲፕሎማቶች የተሳተፉበት ይህ ውይይት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም ሀገራት በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ አውጥተዋል፡፡ የግብጽ ውሃ እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ስዌለም እንዳሉት በአዲስ አበባ የተካሄደው ድርድር…
Read More
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር የሶስትዮሽ ድርድር በአዲስ አበባ ተጀመረ

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር የሶስትዮሽ ድርድር በአዲስ አበባ ተጀመረ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ግብጽ በሱዳን መረጋጋት ዙሪያ ባዘጋጀችው የጎረቤት ሀገራት የመሪዎች መድረክ ላይ በተገኙበት ወቅት ከግብጽ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር በግድቡ ዙሪያ መምከራቸው ይታወሳል፡፡ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ መወያየታቸው ሲገለጽ የግድቡ ውሀ አሞላል ዙሪያ ተወያይተው እስከ መስከረም ወር ድረስ ተቋርጦ የነበረውን የሶስትዮሽ ውይይት ለማስጀመር ተስማምተው ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት ከሁለት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪ የቴክኒክ ባለሙያዎች በግብጽ ካይሮ ተገናኝተው ተወያይተዋል፡፡ ሁለተኛው የሶስትዮሽ ውይይትም ዛሬ በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን የኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን የግድቡ ተደራዳሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በሁለት ተርባይኖቹ ሀይል ማመንጨት የጀመረው የሕዳሴው ግድብ…
Read More
ዩኔስኮ የኢትዮጵያን ሁለት ቅርሶች በዓለም ቅርስነት መዘገበ

ዩኔስኮ የኢትዮጵያን ሁለት ቅርሶች በዓለም ቅርስነት መዘገበ

የባሌ ተራሮች እና የጌድኦ መልክዓምድር በዩኔስኮ ተመዝግበዋል። ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የተመዘገቡ ቅርሶቿን ብዛት ወደ 11 ከፍ በማድረግ ከአፍሪካ በአንደኝነት ተቀምጣለች። የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅትወይም ዩኔስኮ 45ኛ ጉባኤውን በሳውዲ አረቢያ ሪያድ እያካሄደ ይገኛል። በደቡብ ኢትዮጵያ ጌዴኦ ዞን የሚገኘው የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር እና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የዓለም ቅርስ ሆነው መመዝገቡ ተገልጻል። ዩኔስኮ በድረገጹ እንዳስታወቀው የጌድኦ ባህላዊ መልከዓ ምድር እና የብርቅዬ የዱር እንስሳት መገኛ የሆነው የባሌ ብሔራዊ 10ኛ እና 11ኛ ቅርስ ሆነው መመዝገባቸውን ለዓለም አብስሯል። ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 11 ቅርሶችን በዩኔስኮ መዝገብ ስር በዓለም ቅርስነት ያስመዘገበች ሲሆን ከአህጉሪቱ ደቡብ አፍሪካን በመብለጥ በአንደኝነት ትመራለች። ደቡብ አፍሪካ 10 ቅርሶችን ስታስመዘግብ ሞሮኮ ከደቡብ አፍሪካ…
Read More