31
Oct
የገንዘብ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር እና የአየርላንድ መንግሥት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የ8 ሚሊየን 400 ሺሕ ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የፈረሙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ እና የአየርላንድ የዓለም አቀፍ ልማትና ዳያስፖራ ሚኒስትር ዴዔታ ሾን ፍሌሚንግ ናቸው፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱ ሦስት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው 5 ሚሊየን ዩሮ ለሴፍቲ ኔት ፕሮግራም እንዲሁም 3 ሚሊየን ዩሮ በጤና ላይ ያተኮሩ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጽልል። እንዲሁም 400 ሺሕ ዩሮ ደግሞ ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር ድጋፍ እንደሚውል በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ከፊርማ ሥነ- ሥርዓቱ በኋላ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ አየር ላንድ ለኢትዮጵያን የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እያደረገችው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡ ሦስቱም ስምምነቶች በመንግሥት…