መነሻ ገፅ

አሜሪካንን ጨምሮ በርካቶች ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን እያስወጡ ነው

አሜሪካንን ጨምሮ በርካቶች ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሱዳን እያስወጡ ነው

አሜሪካን ጨምሮ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ዲፕሎማቶቻቸውን ከሱዳን ካርቱም ማስወጣት ጀምረዋል፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ በሱዳን ካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶች እና ቤተሰቦቻቸው በዛሬው ዕለት ሀገሪቷን ለቀው መውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዲፕሎማቶቹ የአሜሪካ ጦር ባካሄደው የተሳካ ኦፕሬሽን ከሱዳን ካርቱም በሰላም መውጣት ችለዋል ተብሏል። ፕሬዚዳንት ባይደን ዲፕሎማቶችን ለማስወጣት ለተደረገው የተሳካ ስራ ለኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ እና ሳዑዲ ዓረቢያ መንግስታት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አሁን ላይ በሱዳን የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ አገልግሎት መስጠት እንዳቆመ አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ 150 የሚሆኑ የሳዑዲ ዓረቢያ፣ ግብጽ፣ ካናዳ፣ ሕንድ፣ ኩዌት፣ ፓኪስታን እና የቱኒዚያ ዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት አመራሮች በባህር ከሱዳን ሳዑዲ ዓረቢያ መግባታቸው ተገልጿል። ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ብሪታንያ፣ ስፔን እና ሌሎች ሀገራትም በሱዳን ካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶቻቸውን…
Read More
በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ

በሱዳን ያሉ የውጭ ዜጎችን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ

ኢትዮ ነጋሪ፣ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14 ቀን 2014 ዓ.ም:- ሀገራት ዜጎቻቸውን እያስወጡ ያሉት በጋላባት-መተማ በኩል ነው ተብሏል ዜጎችን የማስወጣት ስራው በካርቱም ካለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ጋር በመነጋገር ነው በሱዳ. ያሉ የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ተጀመረ የተለያዩ ሀገራት በሱዳን ያሉ ዜጎቻቸውን በኢትዮጵያ ድንበር በኩል ማስወጣት ጀምረዋል። በሱዳን ብሔራዊ ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ መካከል የተጀመረው ጦርነት ስምንተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል። ለኢድ በዓል ተብሎ የሶስት ቀን ተኩስ አቁም ቢደረግም ጦርነቱ ዛሬም እንደቀጠለ ነው ተብሏል። ይህ በዚህ እንዳለ የተለያዩ ሀገራት በሱዳን የሚገኙ ዜጎቻቸውን ለማስወጣት ትረቶች ላይ ይገኛሉ። ከካርቱም ዜጎቻቸውን በአየር ትራንስፖርት ለማውጣት ያልተሳካላቸው ሀገራት በየብስ ትራንስፖርት በኢትዮጵያ ድንበር በኩል እያስወጡ መሆኑን ሰምተናል። ሀገራቱ…
Read More
አሜሪካ አንድ ዜጋዋ ሱዳን ውስጥ እንደተገደለባት ገልጸች

አሜሪካ አንድ ዜጋዋ ሱዳን ውስጥ እንደተገደለባት ገልጸች

አንድ የአሜሪካ ዜጋ ሱዳን ውስጥ እየተካሄደ ባለው ውጊያ መገደሉ ተሰምቷል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለፎክስ ኒውስ በሰጠው ቃል ፤ በሱዳን አንድ አሜሪካዊ ዜጋ መሞቱን አረጋግጧል። መስሪያ ቤቱ ፤ ከሟች ቤተሰብ ጋር እየተገናኘ መሆኑንና በደረሰባቸው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል። "በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ለቤተሰብ ካለን አክብሮት የተነሳ ምንም የምንጨምረው ነገር የለም " ሲልም ስለ ሟች ዝርዝር መረጃ ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል። በሌላ በኩል ፤ የአሜሪካ መከላከያ ጦር በአፍሪካ ኮማንድ በኩል በሱዳን ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ መሆኑን አሳውቋል። አሜሪካ በሱዳን ያሉ ዜጎቿን ደህንነት ለማረጋገጥ ወደ ጅቡቲ ተጨማሪ ወታደሮችን ለመላክ እያሰበች መሆኗንም አስታውቃለች። የአሜሪካ ጦር ፤ በካርቱም የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲ ሰራተኞችን እና ዜጎችን ለማስወጣት የሚያስችለውን…
Read More
ኢትዮጵያ ጦሯን ወደ ሱዳን አስገብታለች መባሉን አስተባበለች

ኢትዮጵያ ጦሯን ወደ ሱዳን አስገብታለች መባሉን አስተባበለች

በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ባለችው ሱዳን እስካሁን የተገደሉ ዜጎች ቁጥር ከ350 በላይ አሻቅቧል። ይህ በዚህ እንዳለ የኢትዮጵያ ጦር ወደ ሱዳን ግዛት ገብቶ ወረራ ፈጽሟል የሚሉ ዜናዎች በበርካታ የሱዳን ሚዲያዎች ተዘህበዋል። ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ዛሬ ባወጣችው መግለጫ ምንም አይነት ወታደር ወደ ሱዳን ግዛት አለማስገባቷን አስታውቃለች። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ "በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ግጭት መቀስቀስ የሚፈልጉ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል" ብለዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በመግለጫቸው አንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ እና ሱዳን ግንኙነትን ለማበላሸት በማሰብ፣ "ኢትዮጵያ ወታደሮቿን ሱዳን ውስጥ አስገብታለች በማለት ሐሰተኛ መረጃ እያሠራጩ ነው" ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ውዝግብ ቢኖራቸውም ልዩነታቸው በንግግር ይፈታል ብለው እንደሚያምኑም ገልጸዋል። "ኢትዮጵያ አሁን ሱዳን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ለድንበር…
Read More
በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ በ1 ነጥብ 5 ቢልየን ብር ወጪ የተገነባው “ስቴይ ኢዚ ፕላስ” ሆቴል ወደ ሥራ ሊገባ ነው

በአዲስ አበባ ከአዲሱ ገበያ ከፍ ብሎ እንጦጦ መስመር ላይ የተገነባው፤ "ስቴይ ኢዚ ፕላስ" ሆቴል ከኹለት ሳምንታት በኋላ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ አቶ አሚር ሰኢድ እንዳሉት ሆቴሉ በጥንዶቹ ዳግማዊ መኮንን እና ህይወት አየለ ባለቤትነት የተገነባ ሲሆን ሆቴሉ ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ፈጅቷል ብለዋል፡፡ በአምስት ዓመት ውስጥ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ታስቦ ግንባታው የተጀመረው ይህ ባለ ስምንት ወለል ህንጻ ኮሮና ቫይራ ተጨምሮበት በስምንት ዓመት ውስጥ መጠናቀቁን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ሆቴሉ በባለ አምሰት ኮከብ ደረጃ መገንባቱን የተናገሩት ደግሞ የሆቴሉ ባለቤት እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ወይዘሮ ሂወት አየለ ናቸው፡፡ እንደ ወይዘሮ ሂወት ገለጻ ሆቴሉ በአጠቃላይ 103 ክፍሎች፣ ከ15 እስከ 1 ሺሕ…
Read More
በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ቴሌቪዥኖች ወደ ስርጭት ሊገቡ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ቴሌቪዥኖች ወደ ስርጭት ሊገቡ ነው ተባለ

አምስት የንግድ የቴሊቪዥን ጣቢያዎች የስርጭት ፈቃድ ሊሰጣቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ አምስት የንግድ የሳተላይት ቴሌቪዥን ብሮድካስት አገልግሎት ጣቢያዎች ፈቃድ እንዲሰጣቸው  መወሰኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን አስታውቋል። ፈቃዱን የሚያገኙት ጎህ ቴሌቪዥን፣ ኤፕላስ ቲቪ፣ ሸካል ቲቪ፣ ከገበሬው ቴሌቪዥን እና ኢሲኤን ቴሌቪዥን መሆናቸውን ባለስልጣኑ አስታውቋል። ፈቃድ የሚሰጣቸውም የገንዘብ አቅምና ምንጫቸው ስራውን ለማስኬድ አስተማማኝ እንደሆነ በመታመኑ ነው ያለው ባለስልጣኑ፣ አገልግሎቱን ለመስጠት ድርጅታዊ ብቃት ያላቸው መሆኑ መጣራቱ ተገልጿል፡፡ እንዲሁም የፕሮጀክት ሰነዳቸው፣ ያቀረቧቸው መሳሪያዎችና ቴክኖሎጂዎች አገልግሎቱን ለመስጠት ብቃት ያላቸው መሆናቸው ተጣርቶ መወሰኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ የንግድ ቴሌቪዥን ፈቃድ ለማገኘት የቀረቡ አመልካቾች በባለሥልጣኑ መስሪያ ቤት በመቅረብ ውል እንዲዋዋሉና ከዛሬ ጅምሮ ፈቃዳቸውን መውሰድ እንደሚችሉም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለሁለት የወርቅ አውጪ ኩባንያዎች ፈቀድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለሁለት የወርቅ አውጪ ኩባንያዎች ፈቀድ ሰጠች

ለሁለት ሀገር በቀል ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የደለል ወርቅ ምርት ፈቃድ ተሰጥቷል። የማዕድን ሚኒስቴር ለሁለት ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የደለል ወርቅ የማምረት ፈቃድ መስጠቱን ገልጿል። ፈቃድ የተሰጣቸው ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ እና ኢልኔት ቴክኖሎጂ ግሩፕ የተሰኙት ሀገር በቀል ኩባንያዎች ናቸው። "ቤአኤካ" ፈቃድ የተሰጠው በጋምቤላ ብሄራዊ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ማንግሽ ወረዳ ሲሆን ለፕሮጀክቱ ከ138 ሚሊየን ብር በላይ መመደቡ ተገልጿል፡፡ ይህ ኩባንያ በሚቀጥሉት 4 ዓመታት ውስጥ 911 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ያመርታል ተብሏል። ሌላኛው ፈቃድ የተሰጠው ተቋም "ኢልኔት ቴክኖሎጂ ግሩፕ" ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ አሶሳ እና ሁዱሉ ወረዳዎች እንደሆነ ተገልጿል። ይህ ኩባንያ ለፕሮጀክቱ ከ148 ሚሊየን ብር በላይ መመደቡ አስታውቋል፡፡ የፈቃዱ የአገልግሎት ዘመን…
Read More
በኢትዮጲያ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 7500 ደረሰ

በኢትዮጲያ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 7500 ደረሰ

በሳሙኤል አባተ በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ዓመታት በኮቪድ -19 ከ7 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር አስታውቋል። በኢትዮጲያ በሶስት ዓመት ውስጥ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰው ሲጠቁ ከ7ሺህ 500 በላይ ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው እንዳለፈ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል ። ባለፉት ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በኮቪድ -19 በሽታ 500 ሺ 774 ሰዎች ሲያዙ ከነዚህም ውስጥ 7ሺህ 574 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ተገልጿል ። የኮቪድ-19 ክትባት በሶስት ዙር የተሰጠ መሆኑንና የተፈናቀሉ እና እስረኞች የክትባት ተከታታይ ተጠቃሚነት ላይ ቁጥሩ ዝቅተኛ እንደሆነ በጤና ሚኒስቴር የክትባት ኤክስፐርት የሆኑት ዶ/ር አለማየሁ አየለ ተናግረዋል ። በዓለም ላይ በኮቪድ -19 በሽታ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች እንደሚጠቁ…
Read More
ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመላክ በምልመላ ላይ እንደሆነች ተገልጿል። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴቶች የጅምላ ምልመላ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል ። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች የሳውዲ አረቢያ የሰብዓዊ መብት አያያዟ ደካማ እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴት ሠራተኞች የጅምላ ምልመላ አሳሳቢ ነው ብለዋል፡፡ አሁንም ቢሆን በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች በሳውዲ አረቢያ ከሠራተኛ ሕጎች የተገለሉ እና በዘመናዊ ባርነት ስርዓት ለጥቃት የተጋለጡ ናቸው ተብሏል፡፡ “ካፋላ” በተሰኘው ስርዓት አንድ ሠራተኛ በደል ቢደርስባት እና ከአሠሪዎቿ ብትሸሽ ፓስፖርቷን ጨምሮ የተለያዩ የሰነድ መረጃዎቿን እንድታጣ እንደሚደረግ እና ይህ ስርዓት አሁንም ለውጥ እንዳልተደረገበት ተገልጿል። ‹‹ሳውዲ አረቢያ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በዘፈቀደ በማሰር እና አሰቃቂ…
Read More
ጉምቱው ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ኢዜማን ለቀቁ

ጉምቱው ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ኢዜማን ለቀቁ

አቶ አንዷለም ኢዜማን ተሻጋሪ ለማድረግ የሰነቅነው ህልም ምላሽ ሊያስገኝልኝ አልቻለም በሚል እንደለቀቁ በማህበራዊ ትስስእ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች አንዱ የሆኑት አቶ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል። አቶ አንዷለም ኢዜማን ከመጠንሰስ እስከ መመሥረት፣ ከምሥረታ በኋላም በአባልነት ፓርቲውን በአመራርነት አገልግለዋል። አቶ አንዷለም ለፓርቲው ባስገቡት መግለጫ ላይ በፓርቲው ውስጥ የኢዜማ ስብራት ሲጠገን ለማየት አልቻልኩም ሲሉ ገልጸዋል። በፓርቲው ውስጥ በሚያነሱት ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት ባለመቻላቸው ማዘናቸውን ገልጸዋል። የፓርቲያችንን ቁመናና አሰላለፍ ከወዲሁ እናስተካክል የሚል ተማጽኖ ነበረኝ ያሉት አቶ አንዷለም ፓርቲው ይህንን እድል ሊፈጥር ባለመቻሉ መልቀቂያ ማስገባታቸውንም አክለዋል። ኢዜማ በ2014 በተካሄደው የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ የግዢው ፓርቲ ሁነኛ ተፎካካሪ ነበር። ምርጫው…
Read More