መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ 5000 ዘመናዊ ሩሲያ ሰራሽ ተሽከርካሪዎችን ልታስግባ ነው

ኢትዮጵያ 5000 ዘመናዊ ሩሲያ ሰራሽ ተሽከርካሪዎችን ልታስግባ ነው

የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሰሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት አቶ ብርሃኔ ዘሩ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፤ ተሽከርካሪዎቹ ከሀገሪቱ መልክዓ ምድር ጋር አብረው የሚሄዱ እና የዩሮ 5 የሞተር የተገጠመላቸው በመሆኑ የአየር ብክለት ተፅእኗቸው አነስተኛ ነው። በኢትዮጵያ ያሉ አብዛኛዎቹ ተሽከርካሪዎች ዩሮ 2 እና ዩሮ 3 የሞተር ብቃት ያላቸው ሲሆኑ፤ ሩሲያ ሰራሾቹ ካማዝ ተሽከርካሪዎች ግን በዚህ ረገድ አዲስ ምዕራፍን የገለጡ ናቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር መሆኗ የንግድ አጋጣሚዎችን ለመፍጠር እንዳገዛቸውም ነው የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሰሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንቱ የተናገሩት። ተሽከርካሪዎቹን ወደ ኢትዮጵያ የሚያስገባው የባዝራ ሞተር ድርጅት ማናጀር ያይራድ አስናቀ በበኩላቸው፤ ተሽከርካሪዎቹ በ2025 የመጀመሪያ አጋማሽ ወር ወደ ኢትዮጵያ መግባት ይጀምራሉ ብለዋል። በቀጣይ የሕዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችንም ጭምር ለማስገባት እቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሆነም…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ማድረጉን አስታዉቋል። ይህ ጭማሪ የመጣው መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት አካል እንደሆነ ባንኩ ገልጿል። በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፣ የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣ የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣ የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣ የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ አሳይተዋል። ይሁንና ባንኩ ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ወይም ኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ብድሮች የወለድ ምጣኔው በነበረበት በ12 በመቶ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የውጭ ምንዛሬ የሚያቀርቡ ድርጅቶች ሰራተኞች የግል ብድሮች በስምምነቱ ውል ላይ በመመስረት ከ11 በመቶ እስከ 13 በመቶ የሚደርስ ሲሆን፣ ለየት ያለ ከፍተኛ ዋጋ ላላቸው ደንበኞች ሰራተኞች የግል ብድሮች…
Read More
“ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል”

“ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል”

በክቡር ገና በሀገራችን “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል” የሚል ምሳሊያዊ አነጋገር አለ፡፡ አጋም እሾሀማ ተክል ሲሆን ቁልቋል ደግሞ ለመወጋት የተመቸ ጠፍጣፋ ቅጠል መሰል አካል ያለው ተክል ነው፡፡ አጋሙ በጠንካራ እሾሁ ቁልቋሉን ሲወጋው ልክ ህመሙ ያሰቃየው ይመስል ከጠፍጣፋ አካሉ እንደ እንባ ነጭ ፈሳሽ ያነባል፡፡ እናም “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል” የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ እንደሚኖር ሁሉ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የተጠጋም ሀገር ያለጥርጥር ሲያለቅስ ይኖራል፡፡ ከአይ ኤም ኤፍ ተጠግተው ሲያለቅሱ የኖሩ በርካታ ሀገራትን መጥቀስ ቢቻልም አርጀንቲና፣ ግብጽ፣ ናይጄሪያና ዛምቢያ ጥሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ ተራው የኢትዮጵያ ነው፡፡ በቅርቡም የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂዎሪጄቫ ኢትዮጵያን ጎብኝተው “ በአዲስ…
Read More
የከሰም ስኳር ፋብሪካ በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ከ3 ሺህ በላይ ሠራተኞቹን አሰናበተ

የከሰም ስኳር ፋብሪካ በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ከ3 ሺህ በላይ ሠራተኞቹን አሰናበተ

በአፋር ክልል ዱላሳ ወረዳ የሚገኘው ከሰም የስኳር ፋብሪካ፣ በክልሉ እየተከሰተ ባለው ለወራት የቀጠለ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ይፋ ባደረገ በወሩ፣ ከ3,700 በላይ ሠራተኞቹን ከሥራ ማሰናበቱ ታወቀ። በክልሉ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ በመጣው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ተፈናቅለው በካምፕ የተጠለሉ 3,750 ቋሚና ጊዜያዊ የከሰም ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች፣ የካቲት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ባልጠበቁት ሁኔታ ከሥራ ተሰናብተዋል። ከቻይና ልማት ባንክ በተገኘ 123 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተገነባው ከሰም ስኳር ፋብሪካ ከ10 ዓመት በፊት ነበር ስኳር ማምረት የጀመረው፡፡ በዓመት 260 ሺህ ቶን ስኳር የማምረት አቅም የነበረው ይህ ስኳር ፋብሪካ በአዋሽ አካባቢ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ምክንያት ስራ አቁሟል፡፡ በ20 ሺህ ሄክታር መሬት…
Read More
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በኤርትራ ጉዳይ የሰጡት ሀሳብ የግላቸው እንጂ የመንግስት አቋም አይደለም ተባለ

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በኤርትራ ጉዳይ የሰጡት ሀሳብ የግላቸው እንጂ የመንግስት አቋም አይደለም ተባለ

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ በኤርትራ ጉዳይ የሰጡት ሀሳብ የመንግስት አቋም አለመሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫው ላይ ከጋዜጠኞች ከቀረበላቸው ጥያቄዎች መካከል የቀድሞው የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ሙላቱ (ዶ/ር) ኤርትራን አስመልክቶ ያጋሩት ጽሁፍ ነው። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ከሁለት ሳምንትት በፊት አልጀዚራ ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ "የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት ለመቀስቀስ እየተንቀሳቀሰ ነው፤ በምስራቅ አፍሪካ አዲስ ግጭት እንዳይከፈት ለማስቆም ጊዜው አሁን ነው" ማለታቸው ይታወሳል። የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በኤክስ ገጻቸው ባጋሩት ጽሁፍ በቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የተነሱትን ነጥቦች አጣጥለዋል። ስለ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጽሁፍ ኤርትራ ምላሽ የተጠየቁት አምባሳደር…
Read More
ኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኙ ታሳሪዎች በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም ተባለ

ኢትዮጵያ በእስር ላይ ለሚገኙ ታሳሪዎች በቂ ምግብ እያገኙ አይደለም ተባለ

በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ታራሚዎች በቀን ለአንድ ታራሚ የሚመደበው በጀት 35 ብር ብቻ በመሆኑ በቂ ምግብ እያገኙ እንዳልሆነ ተገልጿል፡፡ የተመደበው በጀት አነስተኛ መሆኑ እና የወቅታዊ የገበያ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ ለታራሚዎች የሚቀርብ ምግብ በቂ እንዳይሆን አድርጎታል ተብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፤ በቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማእከል (በተለምዶ አባ ሳሙኤል) በመባል በሚጠራው ማረሚያ ቤት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ጉብኝት ማድረጉን ተናግሯል፡፡ በዚህም ከምግብ አቅርቦት ማነስ በተጨማሪ አልፎ አልፎ አጃቢ የለም በማለት በቀጠሯቸው ፍርድ ቤት እና ሆስፒታል የማይወሰዱ ታራሚዎች እንዳሉም ባደረኩት ምልከታ ለማወቅ ችያለሁ ብሏል ኢሰመኮ፡፡ የአጃቢዎች እጥረት የሚፈጠረውም በማረሚያ ቤቱ የሰው ኃይል ቁጥር ማነስ እና የመርኃ ግብር መደራረብ…
Read More
ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮችን በሶማሊያ ልታሰማራ ነው

ኢትዮጵያ 2,500 ወታደሮችን በሶማሊያ ልታሰማራ ነው

ኢትዮጵያ እና ግብጽን ጨምሮ አምስት ሀገራት 12 ሺህ ገደማ ወታደሮችን ለማሰማራት ተስማምተዋል የአፍሪካ ህብረት እና የሶማሊያ መንግስት በተልዕኮው በሚሳተፉ ሀገራት ዝርዝር እንዲሁም በሚያዋጡት የወታደር ቁጥር ዙሪያ ከስምምነት ደርሰዋል በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ በሚሳተፉ ሀገራት እና በሚያዋጡት የወታደር ቁጥር ዙሪያ ስምምነት ላይ ተደርሷል ተብሏል። የሶማሊያ ፌዴራል መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ላይ በመወከል ወታደር በሚያዋጡ ሀገራት ቁጥር ላይ መስማማታቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። አትዮጵያ እና ሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ ተስማሙ የሞቃዲሾ መንግስት ከብሩንዲ እና ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ገብቶበት የነበረውን ውዝግብ ተከትሎ የተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር እና የሚልኳቸውን ወታደሮች መጠን ለመወሰን…
Read More
የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሚሰማራ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሚሰማራ ተገለጸ

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ እንዲሳተፍ ተስማሙ፡፡ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንዲሰማራ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መስማማታቸው ተገልጿ፡፡ ከሁለት ቀናት በፊት ወደ ሶማሊያ ያቀኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ  ከሶማሊያ መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኦዳዋ ዩሱፍ ራጌ  ጋር ተገናኝተው በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ስምምነቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሃሙድ በቅርቡ በአዲስ አበባ ያደረጉትን የሁለትዮሽ ውይይት ተከትሎ የተደረገ የቴክኒክ ምክክር አካል ነው ተብሏል፡፡ የጦር መሪዎቹ የሞቃዲሾ ውይይት በቀጠናዊ ደህንነት፣ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምን እና መረጋጋትን የማስጠበቅ አስፈላጊነት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተዘግቧል፡፡…
Read More
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 60 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ እንደሚያካሂድ ገልጿል፡፡ 60 ሚሊየን ዶላር በነገው ዕለት በሁሉም ባንኮች ለጨረታ እንደሚቀርብ ባንኩ አስታውቋል። ባንኩ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራምን ተከትሎ የኢትዮጵያ የውጭ ክፍያ ሚዛን በተለይም የወጪ ንግድ፣ ሐዋላና የካፒታል ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ መሻሻል ማሳየቱን ጠቅሷል። በተለይም ከቅርብ ወራት ወዲህ ወርቅን ወደ ውጭ የመላክ ብቸኛ ሥልጣን ላለው ብሔራዊ ባንክ የሚቀርበው የወርቅ መጠን በመጨመሩ ምክንያት የባንኩ ዓለም አቀፍ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት መጨመሩን ገልጿል። በመሆኑም ከባንኩ የወርቅ ግዥ ጋር በተያያዘ የሚከሰተውን የገንዘብ አቅርቦት ዕድገት ለማገናዘብና በማዕከላዊ ባንኩ እጅ ካለው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከፊሉን ለግሉ ዘርፍ በመስጠት በገበያው ላይ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን ለማሻሻል ባንኩ የተወሰነ…
Read More
ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት የሚያገለግል አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት የሚያገለግል አዲስ ፓስፖርት ይፋ አደረገች

ኢትዮጵያ አራት አይነት ፓስፖርቶችን በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጋለች የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ፓስፖርቶችን ይፋ አድርጓል። ዛሬ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ይፋ የተደረጉት ፓስፖርቶች አራት አይነት ሲሆኑ ከመደበኛ ፓስፖርት በተጨማሪ የዲፕሎማት፣ ውጭ ሀገራት እና የአገልግሎት ፓስፖርቶችም ይገኙበታል። ፓስፖርቶቹ በጃፓኑ ቶፓን የደህንነት ኩባንያ እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ኩባንያ ትብብር ስለመመረቱም ተገልጿል። 10 ዓመት እንዲያገለግል ተደርጎ የተሰራው ይህ ፓስፖርት በአዲስ አበባ በሚገኘው ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተመረተ ነው። የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት መደረግ የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት እንደሚቆጥብ ተገልጿል። ይህ በዚህ እንዳለም በፓስፖርቱ ውስጥ ገጾች ላይ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታዎች የሚያጎለብቱ እና ታሪካዊ ቅርጾችን ይዟልም ተብሏል። እንዲሁም ፓስፖርቱ የማይክሮ ችፕስ የተገጠመለት…
Read More