Tigray

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የኢኮኖሚ ማዕቀብ አራዘመች

አሜሪካ ከሶስት ዓመት በፊት የተቀሰቃሰው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የአሜሪካንን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ይጎዳል በሚል ነበር ጦርነቱ እንዲቆም ጫና ስታደርግ የቆየችው፡፡ ይህ ጦርነት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተደረገ የሰላም ስምምነት ቢቆምም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ግን እንደቀጠሉ ናቸው በሚል ማዕቀቡ ተራዝሟል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ናቸው የተባሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ምስራቅ አፍሪካን እና አሜሪካንን ይጎዳል በሚል የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች፡፡ በዋሸንግተን ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል በኢትዮጵያ ላይ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ ማዕቀብ የሚባል ሲሆን በፈረንጆቹ መስከረም 2021 ላይ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ማዕቀብ ተጥሎ ነበር፡፡ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ይህ ማዕቀብ ከአንድ ዓመት በፊት ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንዲራዘም መፈረማቸው አይዘነጋም፡፡ ፕሬዝዳንቱ ፈርመውበት የነበረው…
Read More
በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ተጠየቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ተጠያቂነት እንዲሰፍን ተጠየቀ

በሁለት አመቱ የትግራይ ጦርነት የተፈፀሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ጥሪ አቀረበ። የያለፈው ጦርነት እና ጥፋት ተጠያቂነት ባለመረጋገጡ በጦርነቱ ተሳታፊ የነበሩ ሐይሎች ለሌላ ጥፋት እየተዘጋጁ ነው በማለት አረና ከሷል። በወቅታዊ የትግራይ ፖለቲካዊ ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙርያ መግለጫ የሰጠው በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነት እና ዴሞክራሲ ህወሓት ውስጥ የተፈጠረው መከፋፈል ለትግራይ አደጋ ይዞ የሚመጣ እና ሐላፊነት የጎደለው አካሄድ እየተከተለ ያለ ሲል ገልፆታል። የዓረና ትግራይ ሊቀመንበር አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ "አሁንም ወደ ጦርነት የሚወስዱ መንገዶች እየታዩ ያሉት እና የጦርነት ነጋሪት የሚጎሰመው ባለፈው 2 ዓመት ለነበረው ጦርነት ከሁሉም ወገን ተጠያቂነት ባለመረጋገጡ ነው፤ ከህወሓት ይሁን ከሻዕብያ እንዲሁም ብልፅግና ወገን የጦርነቱ…
Read More
አሜሪካ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች ወደ ድርድር እንዲመጡ ጠየቀች

አሜሪካ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች ወደ ድርድር እንዲመጡ ጠየቀች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ በአዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ የሚገኘውን የአሜሪካ ግቢ ጎብኝተዋል። አምባሳደሩ በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት የአሜሪካ ግቢ ከ87 አመት በፊት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ከሞት ማምለጫ መሆኑን አውስተዋል። የካቲት 12 1929 ዓ.ም ፋሺስት ጣሊያን በአዲስ አበባ ለሶስት ቀናት ጭፍጨፋ ሲፈጽም አሜሪካዊው ዲፕሎማት ኮርኔልስ ቫን ኤንገርት ከ750 በላይ ኢትዮጵያውያን በኤምባሲው ውስጥ እንዲደደበቁ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያውያን ከ87 አመት የሰውነት ክብራቸው ተጥሶ በህይወት የመኖር መብታቸው ሲነጠቅ ታይቷል ያሉት አምባሳደሩ የሞራል ልዕልና እና ሰብአዊነት ካላቸው ኮርኔልስ ቫን ኤንገርት ልንማር ይገባል ሲሉም ተደምጠዋል። ከ87 አመት በኋላም በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች ሀገራት የሰው ልጆች ክብር እና በህይወት የመኖር መብት በታጣቂዎች፣ ዘራፊ ቡድኖች እንዲሁም በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች መጣሳቸው…
Read More
ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

ህወሃት ታጣቂዎቹ በሱዳን ጦርነት እየተሳተፉ ነው መባሉን አስተባበለ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ "የህወሓት ኃይሎች" ከሱዳን ጦር ጎን በቅጥረኝነት ተሰልፈው ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጋር እየተዋጉ ነው መባሉን አስተባብሏል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በትናትናው እለት ባወጣው መግለጫ የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር እና ተባባሪ ሚሊሻዎች ጋር ሆነው እየተዋጉት እንደሆነ ማረጋገጡን መግለጹን ተከትሎ ነው። የሱዳን ጦርነት ከተጀመረበት ከሚያዝያ 2023 ወዲህ የሱዳን ጦር የውጭ ቅጥረኞችን እርዳታ እየፈለገ ነው የሚል ክስ ያቀረበው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ጦር፣ በጦርነት ወቅት ተገድለው የተገኙ ቅጥረኞችን መመዝገቡን ጠቅሷል። የህወሓት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ጎን ተሰልፈው  እየተዋጉ ነው የሚለውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች "መሰረተ ቢስ ክስ" በጽኑ እንደሚያወግዝ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደገለጸው ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች…
Read More
የአፍሪካ ህብረት በራያ እና አላማጣ የተከሰተው አዲስ ግጭት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአፍሪካ ህብረት በራያ እና አላማጣ የተከሰተው አዲስ ግጭት እንደሚያሳስበው ገለጸ

የአማራ እና የትግራይ ክልል የይገባኛል ጥያቄ በሚያነሱባቸው የራያ አላማጣ እና አካባቢዋ ግጭቶች መከሰታቸውን ተከትሎ የአፍሪካ ህብረት መግለጫ አውጥቷል። መግለጫው የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት በአወዛጋቢዎቹ ራያ አላማጣ፣ ዛታ እና ኦፎላ "በአካባቢው ማህበረሰብ መካከል ያሉ ውጥረቶችን" በትኩረት እየተከታተሉት መሆኑን ገልጿል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረሰው የፌደራል መንግስት እና የህወሓት የዘላቂ ሰላም ስምምነት፣ ሁለቱ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱባቸው "አወዛጋቢ ቦታዎች" በህገመንግስቱ መሰረት እልባት እንዲያገኙ እንደሚደረግ ይጠቅሳል። ሊቀመንበሩ ሁለቱም ወገኖች ግጭት ከማባባስ እንዲታቀቡ እና የአካባቢውን ንጹሃን መፈናቀል እንዲያስቆሙ ጥሪ አቅርቧል። ከአፍሪካ ህብረት በተጨማሪም መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የሰባት ሀገራት ኤምባሲዎች በአማራ እና ትግራይ ከልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ያጋጠመው አዲስ ግጭት እንዳሳሰባቸው አስታውቀዋል፡፡ የካናዳ፣…
Read More
ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

ከአላማጣ እና አካባቢው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ50 ሺህ አለፈ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባወጣው ሪፖርት 50 ሺህ ዜጎች ከራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መፈናቀላቸውን አስታውቋል፡፡ እንደ ድርጅቱ ሪፖርት ከሆነ ከሰሞኑ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላይ ባገረሸው ግጭት ምክንያት ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል ብሏል፡፡ ተፈናቃዮቹ በቆቦ፣ ወልደያ እና ሰቆጣ ከተሞች በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ላይ እንደተጠለሉም ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት ተጨማሪ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የገለጸው ድርጅቱ ለተፈናቃዮች ውሃ፣ ምግብ እና ሌሎች ህይወት ማቆያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑንም ገልጿል፡፡ አሁን ላይ ከለጋሽ ተቋማት እና ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እየተሟጠጠ በመሆኑ በአካባቢው ያለው ማህበረሰብ የሚችለውን ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ለተፈናቃዮቹ መጠለያ፣ የሕክምና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ድጋፎችን ማድረግ ይገባል…
Read More
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከአንድ ዓመት በኋላ ዳግም ተቀሰቀሰ

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከአንድ ዓመት በኋላ ዳግም ተቀሰቀሰ

የትግራይ ታጣቂዎች ወደ አማራ ክልል ዘልቀው ወረዳዎን እና ቀበሌዎችን በሀይል እንደተቆጣጠሩ ተገልጿል፡፡ የአማራ ክልል መንግስት ባወጣው መግለጫ ህወሓት በፕሪቶሪያ የተፈረመውን የዘላቂ የሰላም ስምምነት በመጣስ ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ፈጽሞብኛል ሲል ከሷል። በፌደራል መንግስት በኩል ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር ውይይት ለማድረግ መጣሩን የገለጸው ክልሉ፣ ህወሓት የሰላም አማራጮችን ወደ ጎን በመተው በስምምነት አወዛጋቢ ተብለው የተለዩትን የራያ አላማጣ፣ የራያ ባላ፣ የኦፍላ፣ የኮረም እና ዛታ አካባቢዎችን ወርሯል ብሏል። የክልሉ መንግስት እንዳለው ህወሓት ለአራተኛ ዙር ወረራ በመፈጸም በህወሓት እና በፌደራል መንግስት መካከል ከተካሄዱት "ከባለፉት ሶስት ዙር ደም አፋሳሽ ጦርነቶች" አለመማሩን የሚያሳይ ነው። የአማራ ክልል ወረራ ተፈጽሞባቸዋል ያላቸው ቦታዎች እና የወልቃይት፣ ጠገዴ እና ጠለምት በ2013 ጦርነት ከመቀስቀሱ…
Read More
አፍሪካ ህብረት በፕሪቶሪያ የተፈረመው የኢትዮጵያን የሰላም ስምምነት መገምገም ጀመረ

አፍሪካ ህብረት በፕሪቶሪያ የተፈረመው የኢትዮጵያን የሰላም ስምምነት መገምገም ጀመረ

በዚህ ግምገማ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት፣ ህወሃት፣ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር እና ሌሎችም ተገኝተዋል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመታት በዘለቀው ጦርነት የአፍሪካ ህብረት በደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ጦርነቱ መቆሙ ይታወሳል፡፡ ይህ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን በስምምነቱ መሰረት ያልተፈጸሙ ጉዳዮች እንዳሉ በሁለቱም ወገኖች ሲነሳ ቆይቷል፡፡ አፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተደረሰውን የፕሪቶሪያ የተኩስ ማቆም ስምምነት አፈፃፀም ስትራቴጂካዊ ግምገማ እያካሄደ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል። የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በኤክስ ገፃቸው ባጋሩት መልእክት የአፍሪካ ህብረት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት…
Read More
ጦርነት እና የማህበራዊ መረዳጃ ተቋማት ስብራት በትግራይ

ጦርነት እና የማህበራዊ መረዳጃ ተቋማት ስብራት በትግራይ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ተሰባስቦ ተረዳድዶና ተደጋግፎ መኖር በአጠቃላይ ማህበራዊ ሕይወት አንዱ የሕይወት ዑደት ነው።  ታዲያ ይህ የመረዳዳት ሒደት ደስታን ሐዘንን እንዲሁም የጤና እክልን መሠረት በማድረግ የሚከወን ነው በተለይም እድር እና እቁብን እንደ ምሳሌ ብንወስድ ኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ የሚባሉ እና ማህበረሰቡ ጠብቆና አክብሮ የያዛቸው መረዳጃ እና መደጋገፊያ ሕብረቶችናቸው። ታዲያ እነዚህ ሕብረቶች በአንድም በሌላም መልኩ እክል ሲገጥማቸው አሊያም የመፍረስ አደጋ ሲጋረጥባቸው ለመታደግ ጊዜ የሚፈጅ እና አስቸጋሪ ይሆናል። በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ከዛም በፊት በነበረው የኮሮና ወረርሺኝ እንዲህ ያሉ መረዳጃ ማህበራትን ለማጥፋት አሊያም ለማቀዝቀዝ ዋነኛ ምክንያቶች ሆነዋል። በመቀሌ ከተማ የሚገኝ ትልቅ እድር ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ለተኪዳን በነዚህ ሁለት አጋጣሚዎች የተፈጠረውን የእድሩን ከፍተኛ መቀዛቀዝ ሲገልጹ…
Read More
ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ ለተረጂዎች ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

በኢትዮጵያ እያሻቀበ ላለው የተረጂዎች ቁጥር ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ መንግስት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች የምግብ ርዳታ ለማቅረብ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የኢትዮጵያ መንግሥት በጋራ ባወጡት ሪፖርት ላይ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ አታለለ አቡሃይ፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው የተረጅዎች ብዛት 6 ነጥብ6 ሚሊዮን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የተፈጥሮ አደጋዎች፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ ጦርነት እና ሌሎች አደጋዎች ምክንያት የተፈናቃዮች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል፡፡ የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ካደረጉ በኋላ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም አሳሳቢ የምግብ…
Read More